በመጀመሪያ ዲግሪ (Post Basic)ጤና ሳይንስ ፕሮግራም ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በ2014 የትምህርት ዘመን በዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አዲስ ከፋይ (self-sponsor) የመጀመሪያ ዲግሪ በ Post Basic ፕሮግራም በቀን በተለያዩ ትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ  አመልካቾች ከመስከረም 26 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 05 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሬጅስትራር በመቅረብ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

 

የትምህርት መስኮቹ/ፕሮግራሞቹ፣

Surgical Nursing 

Family health 

Psychiatric Nursing 

Operating theatre Nursing 

Neonatal Nursing 

Anesthesia 

Pharmacy 

Medical Laboratory Technology 

Health Informatics 

Pediatric Nursing 

Midwifery 

Human Nutrition ( generic 4 year)

Nursing 

የመግቢያ መስፈርት

  • እውቅና ካለው ኮሌጅ በዲፕሎማ ወይም በደረጃ 4 ዲፕሎማቸውን በሚያመለክቱበት የትምህርት ዘርፍ ተዛማጅ በሆነ ትምህርት ያጠናቀቁና የደረጃ 4 ብቃት ማረጋገጫ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
  • የመሰናዶ ፈተና የወሰዱ እና የሣይንስና ከፍተኛ ሚኒስቴር በየአመቱ የሚያወጣውን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ የሚያሟሉ(ለ Human Nutrition አመልካቾች ብቻ )
  • በተጨማሪ በስርአተ ትምህርቱ ላይ ያለውን መስፈርት የሚያሟሉ

ማሳሰቢያ

ለማመልከት

  • የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና ፎቶኮፒ ማቅረብ
  • የማመልከቻ ማይመለስ ብር 100.00 መክፈል

ሲሆን የሚጠበቅባችሁን መስፈርትና ፈተናውን ያለፋችሁ አመልካቾች እስከ ምዝገባ ጊዜ official transcript ማስላክ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ለተጨማሪ መሪጃ

በስልክ መስመር 251-118704615 ዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በመደወል ወይም በ ኢሜል አድራሻ፡ mhmc@kmu.edu.et መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ

                                                   ሬጅስትራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬትe

Posted in Uncategorized.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *