በ2014 ዓ.ም ወደ ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ሚያዝያ 28 እና 29/2014 ዓ.ም ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ወደ ዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ
- የ1ዐኛ እና 12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሰርተፊኬት
- ከ9-12 ክፍል የተማራችሁበትን ትራንስክሪፕት
- 4 ፓስፖርት ሳይዝ ፎቶግራፍ
- አንሶላና ብርድልብስ
- የስፖርት ልብስና ጫማ
ይዛችሁ እንድትመጡ እያስታወቅን ከላይ ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጡ ተማሪዎችን የማናስተናግድ መሆኑን እናስታውቃለን።