የ2016 ዓ.ም ልዩ የክረምት መርሐግብር የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመውሰድ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ሰልጣኞች በሙሉ፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር ለልዩ የክረምት መርሐግብር የአቅም ግንባታ ስልጠና እንድትወስዱ በዩኒቨርሲቲው የተመደባችሁ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ምዝገባ እንደሚካሄድ አውቃችሁ፣ በዕለቱ በዩኒቨርሲቲው በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ከተጠቀሰው ዕለት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ሰልጣኝ በምንም ሁኔታ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ

ወደ ዩኒቨርስቲው ስትመጡ ፦

    1. ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ
    2. ከኦሮሚያ የምትመጡ ሰልጣኞች የራሳችሁን ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የትራስ ጨርቅ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡
    3. ከአዲስ አበባ የምትመጡ በተመላላሽነት ስለምትስተናገዱ የተጠቀሱትን ጉዳዮች ማምጣት አይጠበቅባችሁም።
    4. ከኦሮሚያ የምትመጡ ሰልጣኞች በዕለቱ ከ 2:30-3:30 ከአዲስ አበባ የምትመጡ ደግሞ ከ6:30 -7:30 ሰዓት በዩኒቨርሲቲ ግቢ ተገኝታችሁ ምዝገባ እንድታከናውኑ ፤
    5. ከአዲስ አበባ የምትመጡ ለመኝታ እና ለምግብ የተያዘላችሁ በጀት በካሽ የሚሠጣችሁ ይሆናል።

                                                                                                                                                          ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ

Posted in Uncategorized.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *