(ማክሰኞ 27/07/2014)
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት በተከበሩ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና ሰብሳቢነት በዩኒቨርሲቲው ፍኖተ-ካርታ ላይ በሠፊው መክረው በሂደቱም ላይ የነበረው ምቹ ሁኔታ እና ተግዳሮቶች ውይይት ተደርጎባቸው መግባባት የተደረሰባቸው ሲሆን፣ ሰነዱ በተሠጠው ግብዓት ዳብሮ ለውሳኔ ለትምህርት ሚኒስቴር እንዲቀርብ ሆኗል።
በሌላ በኩል ዩኒቨርሲቲው የመምህራን ማህበር ለማቋቋም የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ የመነሻ ሀሳቡ በጊ/የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ ቀርቦ የመምረጫ ጊዜ ሠሌዳ ተቀምጦ ስብሰባው ተጠናቋል።
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት