በላቴክስ ሶፍትዌር አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ሥልጠና ለመምህራን ተሰጠ።

 

ለጥናት እና ምርምር አጋዥ በሆነው ላቴክስ (Latex) የመተግበሪያ ሶፍትዌር አጠቃቀም ዙሪያ ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን በፊዚክስ ላብራቶሪ ሚያዝያ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ሥልጠና ተሰጥቷል።

ሥልጠናውን ለመምህራኑ የሰጡት ዶ/ር ደረሰ ተርፋ ሲሆኑ፣ ሥልጠናው በተካሄደበት ወቅት እንደገለጹት፣ ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን የተሰጠው ይህ ሥልጠና፣ ለጥናት እና ምርምር፣ መጽሐፍ ለማዘጋጀት፣ ሪፖርት ለመፃፍ እና ለማቅረብ አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል።

ምንም እንኳን ሥልጠናው በመጀመሪያ ዙር ለሳይንስ መምህራን ቢዘጋጅም፣ በቀጣይ ለሌሎች የዩኒቨርሲቲው መምህራን ደረጃ በደረጃ የሚሰጥ መሆኑን ዶ/ር ደረሰ ጠቁመዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

 
 
 
 
Posted in Office of the Communication Affairs.

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *