የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት የበጎ ፈቃደኝነት ቀን የሆነውን ጳጉሜ አንድ ምክንያት በማድረግ ችግኝ ተከሉ፡፡

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት የበጎ ፈቃደኝነት ቀን ምክንያት በማድረግ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ በተዘጋጁ ስፍራዎች ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ፍራፍሬ ችግኞችን ጭምር ዛሬ ጳጉሜ 1/2014 ዓ.ም ተክለዋል፡፡
የችግኝ ተከላው ስነስርዓት በተጀመረበት ወቅት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፣ ጳጉሜ አንድ ቀን የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በመሆኑ ወደን ፈቅደን የምንሰራበት፣ ወደን ፈቅደን ችግኝ የምንተክልበት፣ ወደን ፈቅደን ሀገራችንን ከወራሪው ኃይል የምንከላከልበት ቃል የምንገባበት ነው ብለዋል፡፡ ወንድሞቻችን የመከላከያ ሠራዊት አባላት በግንባር እየተፋለሙ እና ለሀገራቸው የህይወት መስዋዕት እየከፈሉ መሆናቸውን የጠቀሱት ፕሬዝዳንቱ፣ እኛ ደግሞ በአንድ በኩል ልማቱን እያሳለጥን በሌላ በኩል ለሀገር መከላከሉ ደጀንነታችንን የምናረጋግጥበት ነው ብለዋል።
ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ከተንከባከብነው ለትውልድ የሚተላለፍ፣ ድርቅን በመከላከል የሀገራችን ምህዳር የተሻለ የሚያደርግ ጠቀሜታውም ዘርፈ ብዙ ነው ያሉት
ዶ/ር ብርሃነመስቀል አያይዘው የወለደችንና ያሳደገችን እናት ሀገራችን ለኛ ችግኛችን ናት ልንጠብቃት ልንንከባከባት ይገባል ለዚህም በዚህ አጋጣሚ በግንባር ሆኖ መስዋዕትነት እየከፈለ ካለው መከላከያችን ጎን መሆናችንንና ለሚጠበቅብን ሁሉ አለኝታችንን እናረጋግጣለን ብለዋል።
በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የግቢ ውበት እና መናፈሻ ሥራ ኃላፊ አቶ ግርማ ከፍያለው በዚሁ ጊዜ ስለ ችግኝ አተካከል ገለፃ የሰጡ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት የተተከሉትን 600 ችግኞች ጨምሮ በዘንድሮው ዓመት 18 ሺህ ልዩ ልዩ ችግኞች በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡
ከተተከሉት ችግኞች መካከል ጓሳ የተሰኘ የሣር ዝርያን ጨምሮ አፕል (ፖም)፣ አቦካዶ፣ ፅድ፣ አልተርናታ፣ ሳይፕረስ እና ስፓቶዲያ እንደሚገኙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
                                     ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 6 people, people standing, tree and grassMay be an image of 5 people, people standing and outdoors

Gender, Children, and Youth Directorate Delivers Training on Life Skills to Students

In collaboration with the Union of Students, Gender, Children and Youth Directorate (GCYD) delivered comprehensive, interactive training on life skills to the students of Kotebe University of Education (KUE) today, on the 3rd of September 2022, at the main, basically focusing on psychological, social, communicational, vocational, mental and physiological skills.
At the event, Dr. Fikirte W/Silassie, the Director of the GCYD remarked that the training would help the students not only for their academic success in the University but also elsewhere after graduation in their life. Dr. Fikirte also reminded the trainees that life skills could not be mastered in a training session or overnight; hence, she advised them that they should be aware of the importance of life skills and keep on learning them to be fruitful in their life.
It was learnt that the training was held bilingually to help the trainees to grasp the essences and contents of the training in the languages they understand and communicate better. The trainees were also made to express their opinions on what they think they are talented for and their experiences as well.
                                   Communications Affairs Directorate

በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በስታትስቲክስ የትምህርት መስክ የሦስተኛ ዲግሪ (Ph.D) የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ የአፕል ችግኝ ተከሉ፡፡

በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በስታትስቲክስ የትምህርት መስክ የሦስተኛ ዲግሪ (Ph.D) የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ የአፕል ችግኝ ተክለዋል፡፡ በዚሁ ወቅት የአካዳሚክ ጉዳዮች ጊ/ም/ፕሬዝዳንት ዶክተር ሽመልስ ዘውዴ እንደተናገሩት፣ ይህ አይነቱ የችግኝ ተከላ ተግባር ከፒ. ኤች.ዲ ተማሪዎች የሚጠበቅ መልካም አርአያነት መሆኑን በመጥቀስ፣ የአፕል ፍሬው እስኪደርስ ድረስ ተማሪዎቹ በግቢው ውስጥ ሊቆዩ ስለሚችሉ ተንከባክበው ለፍሬ ማብቃት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል፡፡
የችግኝ ተከላው ስነስርዓት በተካሄደበት ውቅት በስታትስቲክስ የትምህርት መስክ የሦስተኛ ዲግሪ መርሐግብር የተማሪዎቹ መምህር የሆኑት ዶ/ር አየለ ታዬ እንዳሉት ተማሪዎቹ ቀደም ሲል በእንጦጦ አካባቢ ችግኝ መትከላቸውን አስታውሰው በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢም ተመሳሳይ የችግኝ ተከላ ማከናወናቸው በምሳሌነት የሚታይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት የችግኝ መትከያ ቦታውን ስለፈቀደላቸውም አመስግነዋል፡፡
ተማሪዎቹ ከመምህራቸው ጋር በመሆን የተከሉትን 15 የአፕል ችግኝ ለሦስት ሺህ ብር በላይ በማውጣት በራሳቸው ወጪ የገዙ ሲሆን፣ የችግኝ ተከላውን ሂደትም የፋሲሊቲ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደምስ አባተ ከተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት እና ከዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች ጋር በመተባበር ያመቻቹ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
                             የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 10 people, people standing, tree and sky

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተቋማዊ የሽግግር ሰነዶች ላይ ከመምህራን ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተቋማዊ የሽግግር ሰነዶች ላይ ከመምህራን ጋር ዛሬ 23/12/2014 ዓ.ም. በዋና ግቢ ውይይት አካሄዷል፡፡ የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት አብይና ቴክኒካል ኮሚቴ ተዋቅሮ ሰፋ ያለ ጊዜ ተወስዶ ሲዘጋጅ የቆየው የዩኒቨርስቲው ምስረታ ፍኖተ ካርታው እና የካሪኩለም ማዕቀፍ ከመነሻው ጀምሮ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ እንዲሆን ተደርጓል። በዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና የዘርፉ ከፍተኛ ምሁራን፣ የቦርድ አመራሮች ፣ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል ወዘተ ተወያይተውበት ግብዓት ሰጥተውበታል።
ፕሬዚዳንቱ አያይዘው እንዳሉት እየተዘጋጀ ያለው ፍኖተ ካርታ እና የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ በአጠቃላይ የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት ችግር እና ክፍተት ለመሙላት ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ከራሳችን ጀምረን ክፍተቱን የሚያርም ዝግጅት ማድረግ ይጠበቅብናል፤ በመሆኑም የዩኒቨርሲቲው መምህራን ለአዲሱ ተልዕኮአችን ብቁነታቸውን ማረጋገጥ ፤ ራሳቸውን ማዘጋጀት ፤ “ማነው መምህር ?” የሚለውን መመለስ ይጠበቅባቸዋል። ለዚህ መሠረታዊ ጉዳዩ ከቀደመው አስተሳሰብ ወጥቶ በአዲስ እይታ አዲሱን ሀገራዊ ተልዕኮና ኃላፊነት በአዲስ አስተሳሰብ መቀበልና ለዚያ ትግበራ ብቁ ሆነው ለመገኘት የትምህርት ዩኒቨርሲቲዎችን ልምድ ማየትና መረዳት አለብን ብለዋል ።
ለስኬቱም ተቋሙ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች፣ የትምህርት ቢሮዎች ፣ የፌዴራል እና የክልል የሥልጠና ተቋማት ቀጥተኛ ባለድርሻዎቻችን ናቸው። ከዚህም አንፃር ከባለድርሻ አካላቱ እንዲሁም ከዘርፉ ምሁራን ጋር ቅንጅት በመፍጠር የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮንም በመቀመር ሰነዶቹን የበለጠ ማዳበር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ጊ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ እንደተናገሩትም፣ ዩኒቨርሲቲው አዘጋጅቶ በተለያዩ መድረኮች ለባለድርሻ አካላት ለውይይት ካቀረባቸው ሰነዶች መካከል የተቋሙ የሽግግር ፍኖተ ካርታ እና የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ ላይ የዩኒቨርሲቲው መምህራን እንዲወያዩባቸው መድረኩ የተዘጋጀው ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ትግበራ የሚገባ በመሆኑ መምህራኑ በቂ ግንዛቤ በመጨበጥ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለማስቻል እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ዶ/ር ፈቀደ ቱሊ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ የተቋሙ የሽግግር ፍኖተ ካርታ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ብቸኛው የሀገሪቱ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን በአዋጅ ከተወሰነበት ጊዜ ጅምሮ በተሰጠው ኃላፊነት መሠረት ሰነዱ የትምህርት ጥራት ችግርን በሚፈታ እና ሁለንተናዊ የትምህርት አካሄድን በሚያግዝ መልኩ መዘጋጀቱን ለውይይቱ ተሳታፊዎች አብራርተዋል፡፡ ዶ/ር ኤፍሬም ተክሌ በበኩላቸው የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፉ የዩኒቨርሲቲውን አጠቃላይ የመማር ማስተማር ሂደት የሚመራ ሲሆን፣ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መዘጋጀቱን እና በተለያዩ ባለድርሻ አካለት በተለያዩ ጊዜያት ውይይት የተደረገበት መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው መምህራንም በበኩላቸው በቀሩት የዩኒቨርሲቲው ተልዕኮ፤ የትምህርት መርሀግብሮችና ስያሜዎቻቸው እንዲሁም በተማሪዎች አቀባበል ሁኔታዎች ላይ በማተኮር ሰፊ ገንቢ ሀሳቦችን በማንሳት በውይይቱ ላይ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል፡፡
                                የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 3 people, people sitting and indoorMay be an image of 7 people and people sitting

KUE’s Electoral Committee Members Devote Even Their Weekend Time to Finalise the Vice-presidential Election Process

KUE’s electoral committee members are busy dealing with finalising the vice-presidential election processes as per their promise even devoting their weekend time. This truly witnesses their commitment.
                                         Communications Affairs Directorate
                                                 Sunday, 28/08/2022
May be an image of 7 people

KUE Casts a Vote on Vice Presidency for Its Two Positions

Kotebe University of Education (KUE) cast votes on the shortlisted candidates for Academic Affairs and Administration and Development vice presidents’ positions at the event held today, on the 27th of August 2022, at its main campus. The Governing Board, Senate and Council members of the University and representatives from academic and administrative staff and students’ union representatives participated in making decisions on the recruitment of the vice presidents for the aforesaid positions led by the electoral committee.
At the onset of the event, the electoral committee chairperson, Professor Yalew Endawoke, urged the electorates to be free, fair and rational in evaluating the potential of the candidates based on only and only the essence of the strategic plans presented, nothing else, towards the institution’s merits. As to the remarks of the chairperson, five candidates were shortlisted for each position based on the criteria set to evaluate their applications though afterwards some of them resigned for anonymous personal reasons.
The candidates were subsequently given ten minutes each to present their thought-to-be institutional strategic plans which were followed by explanations to questions posed by the attendees. The attendees were made to rate the ideas presented by the candidates based on the checklist set for the same purposes. Eventually, the electoral committee chairperson guaranteed electorates that the committee would fairly compute the cumulative results of the candidates’ experiences, qualifications and presentations, and then announce the winners shortly.
It was observed that 4 candidates competed for the Academic Affairs and two others ran for the Administration and Development vice presidents’ positions. Participants also noted that the free and fair election of the to-be-leaders was the first of its kind in KUE’s experience.
                                                                               Communications Affairs Directorate
May be an image of 1 person and indoorMay be an image of 1 person and text that says 'fessional preparation and werke context of my strategic plan als and strategic actions'May be an image of 1 person, standing and text that says 'KMU 2016 KUE 2022'
May be an image of 1 person and standingMay be an image of 6 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of 4 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of 3 people, people sitting and indoor

የቀድሞ የኮተቤ ትምህርት ኮሌጅ ተማሪ ዶ/ር አብረሃም አለሙ ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መጻሕፍትን ለገሱ፡፡

የቀድሞ የኮተቤ ትምህርት ኮሌጅ ተማሪ እና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መኖሪያቸውን በውጭ ሀገር ያደረጉት ዶ/ር አብርሃም አለሙ ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ነሀሴ 12/2014 ዓ.ም 709 መጻሕፍትን ለግሰዋል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በመጻሕፍት ርክክብ መርሀግብሩ ላይ እንደገለፁት፣ ዶክተር አብርሃም አለሙ ለዩኒቨርሲቲው ያበረከቱት መጻሕፍት ለትውልድ እና ለሀገር የሚጠቅሙ በመሆናቸው ትልቅ ግምት የሚሰጣቸው ናቸው፡፡ በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተሰማሩበት መስክ የሙያ እና የቁሳቁስ ድጋፍ ቢያደርጉ፣ ይህንንም በጎ አድራጎት አንዱ ለሌላው ቢያስተዋውቅ እና አንድ ላይ ብናብር ሀገራችን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ወደተሻለ ደረጃ ልናሸጋግራት ይቻላል ያሉት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፣ ዩኒቨርሲቲው ከዩኒቨርስቲው የዕውቀት ማዕድ ተቋዳሾች ዶ/ር አብርሃምን ሁሌም እንደሚያስታውስ እና እርሳቸውም ሌሎችንም ሀገር ወዳድ ዜጎቻችንን በማስተባበር በቀጣይም ዩኒቨርስቲውን የመደገፍ ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አድርገውላቸዋል።
በሥነስርዓቱ ላይም ዶክተር አብርሃም አለሙ እንደተናገሩት በ1974ዓ.ም ሰኔ 29 ቀን ከኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በዲፕሎማ መርሐግብር መመረቃቸውን አስታውሰው፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በመምህርነት እያገለገሉ መሆናቸውን በማውሳት የዛሬ መሠረታቸው ለሆነው ኮትዩ ያበረከቱአቸውን መጻሕፍት በነዚሁ የአገልግሎት ዘመናቸው ከሀገር ውስጥ እንዲሁም ለዶክትሬት ዲግሪ ትምህርት ወደ ሆላንድ በሄዱበት ጊዜ ከውጭ ሀገር የገዟቸውና ያሠባሠቧቸው መሆናቸውን አስታውሰዋል፡፡
መጻሕፍቱ በኢትዮጵያ ስነጽሑፍ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ድርሰት የሆነውን ጦቢያ ጨምሮ በስነጽሑፍ፣ በቋንቋ፣ በፎክሎር ንድፈ ሐሳብ፣ በአንትሮፖሎጂ፣ በታሪክ እና በሌሎች የሶሻል ሳይንስ የትምህርት መስኮች ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን የጠቀሱት ዶ/ር አብርሃም አለሙ፣ “ለዓመታት ያህል አብረውኝ የቆዩትን መጻሕፍት ለተማርኩበት ለቀድሞው የኮተቤ ትምህርት ኮሌጅ ለአሁኑ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመስጠቴ ታላቅ ደስታ ይሰመኛል” ብለዋል፡፡ መጻሕፍቱን ለመረከብ የዩኒቨርሲተው ኃላፊዎች ላደረጉት ትብብርና ቤተሰባዊ አቀባበል አመስግነዋል፡፡
በመጨረሻም ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና እና ዶ/ር አብርሃም አለሙ በጋራ በመሆን መጻሕፍቱን ለኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ቤተመጻሕፍት እና ዶክመንቴሽን ዳይሬክተር ለሆኑት ለአቶ ገብረመስቀል ግርማ ያስረከቡ ሲሆን፣ ዶ/ር አብርሃም አለሙ ላበረከቱት አስተዋፅዖም በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና አማካኝነት የእውቅና የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
                                 የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 10 people and people standing

KUE Crafts Its New Five Years’ Strategic Plan

In endeavouring to craft its five years new strategic plan, KUE conducted a two-day fruitful consultation workshop with EDT, an international organisation not-for-profit, from August 8 to 9, 2022. During the workshop, international experiences had been thoroughly reviewed and contextualised to the vision, mission, and mandate of the University.
At the event, EDT’s high-profile professionals delivered invaluable technical support to the KUE’s team in ideating, thematising, refining and contextualising, and gearing the contents of the strategic plan toward addressing the relevance, access, quality, and equity of education in Ethiopia.
It is evident that KUE, as a national flagship university of education,capitalises on producing competent and effective education professionals to transform the education systems of Ethiopia.
                                        Communications Affairs DirectorateMay be an image of 6 people, people sitting and indoor
May be an image of 6 people, people sitting and people standing
May be an image of 4 people, people sitting and outdoorsMay be an image of 3 people and people sitting

KUE Hosts A Joint Workshop on Designing State-of-the-Art Teachers and Leaders Development Programmes

A two-day workshop which was jointly organised by Kotebe University of Education (KUE) and Education Development Trust (EDT) was launched today, on the 4th of August 2022 at Yod Abyssinia International Hotel. The workshop’s focus was to train KUE’s professionals on designing state-of-the-art teachers’ and educational leaders’ development programmes.
Three high-profile professionals, Dr Clare Buntic, Marion Smallbones, and Maggie Farrar from the UK, have delivered very interactive training through face-to-face and online blended approaches. At the event, Dr. Berhanemeskel Tena, the President of KUE, remarked that the workshop would eminently contribute to the achievement of the institutional mission. The President was also grateful for the contributions made to KUE by EDT in general and the professionals who delivered the training in particular.
It was learnt that KUE and EDT had signed an MoU to mainly work on developing co-funding proposals, establishing KUE’s Research and Innovation Centre, collaborating on research programmes, providing school-based training, improving the quality of education, and providing technical support in the development of career progression frameworks. It was said that the agreement would also focus on developing innovative and practice-based curricula, building the capacity of leaders through mentoring, coaching, and supporting KUE in implementing the strategic plan to achieve its mission.
                                              Communications Affairs Directorate

KUE ESTABLISHES A PARTNERSHIP AGREEMENT WITH EDT

Kotebe University of Education (KUE) signed a memorandum of understanding (MoU) with Education Development Trust (EDT) on July 21, 2022. The agreement enables KUE to receive technical assistance and advisory support, which would contribute toward the University’s mission accomplishment.
In the agreement signing ceremony, Dr Berhanemeskel Tena, the President of KUE, remarked that the partnership would help KUE to excel in large-scale collaborative research that brings more relevant and informative findings, which is one of its primary focuses. Dr Berhanemeskel also emphasized the fact that the professional support the KUE staff gain from the EDT would mitigate the problems that the education sector currently experiences.
Dr Abdu Zeleke, EDT’s Country Representative, on his part, expressed his delight in engaging in a professional partnership with KUE. He added that the partnership would continue to exist. The representative further said that EDT is ready to go beyond its plan and offer professional and expertise-based services to KUE.
It was also revealed at the event that KUE would acquire services which include consultation on the implementation of its institutional plans and financial aids.
                                     Communications Affairs Directorate
May be an image of 3 people and people standing
May be an image of 2 people and people standing
May be an image of 2 people, people sitting and people standing
May be an image of 2 people, people sitting, people standing and suit