በኮትዩ የአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ለዕይታ ቀረበ።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል ተማሪዎች ከመምህራኖቻቸው ጋር በመተባበር ያዘጋጇቸውን የኪነ ህንጻና ሌሎች ዲዛይኖች የያዘ ኤግዚቢሽን በዩኒቨርሲቲው አዲሱ ጂ + 8 ህንጻ ግንቦት 24/2014 ዓ.ም ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ዕይታ አቅርቧል።
የኮትዩ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር ሙህዲን ሙሃመድሁሴን ኤግዚቢሽኑን በከፈቱበት ወቅት እንደተናገሩት፣ የትምህርት ትልቁ ጥቅም እውቀትን መያዝ ብቻ ሳይሆን ከትምህርት የተገኘውን እውቀት ወደ ተግባር መለወጥ በመሆኑ፣ በአርክቴክቸር ከመምህራኖቻቸው ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ኤግዚቢሽን በጣም የሚደነቅ እና የሚበረታታ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የከተማ ልማት ጥናት ፋካልቲ ዲን ዶ/ር ይፍሩ ዋቅቶሌ በበኩላቸው፣ ይህ ኤግዚቢሽን በተማሪዎች መዘጋጀቱ ለሚቀጥሉት ተማሪዎች ከፍተኛ ተነሳሽነት የሚፈጥር በመሆኑ፣ በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉ ተማሪዎችን እና መምህራንን አመሰግናለሁ ብለዋል።
የአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት አቶ ስንታየሁ ዓለምነው ኤግዚቢሽኑ በአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል የመጀመሪያው መሆኑን ገልጸው፤ ተማሪዎቹ በንድፈ ሃሳብ እና በተግባር ያገኙትን እውቀት አዋህደው ልዩ ልዩ ዲዛይኖችን እና የኪነ ህንፃ ጥበቦችን ለአውዳ-ሪዕዩ ማቅረብ ችለዋል ብለዋል።
የኮትዩ የግንባታና መሠረተ ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍሬው ዘሪሁን የአርክቴክቸር ትምህርት ክፍሉ የዛሬ አምስት አመት ሲከፈት የመጀመሪያ ተቀጣሪ እና የትምህርት ክፍሉ ኃላፊ እንደነበሩ አስታውሰው፣ ትምህርት ክፍሉ ይህን መሰሉን ጥሩ ኤግዚቢሽን የማዘጋጀት ደረጃ ላይ በመድረሱ በጣም ደስተኛ ነኝ ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በኤግዚቢሽኑ ዝግጅት ላይ በመገኘት ተማሪዎቹን ያበረታቱ ሲሆን የኤግዚቢሽኑ አዘጋጅ ተማሪዎች ያቀረቧቸውን የኪነ ህንፃ ንድፍ ስራዎቻቸውን በተግበር መሬት ላይ በማሳረፍ አሻራዎቻቸውን ለሚቀጥለው ትውልድ መተው እንዲችሉ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ ውስጥ የግንባታ ቦታ እንደሚያመቻቹላቸው ቃል ገብተዋል፡፡ በዚሁ ወቅት ተማሪዎች የንድፍ ስራዎቻቸው ውጤት ያሆነውን ስጦታ ለፕሬዝዳንቱ አበርክተዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ልዩ ልዩ የኪነ ህንፃ ዲዛይኖች፣ የጥበብ ቅቦች እና ምስሎች የቀረቡ ሲሆን፣ እነዚህ ሥራዎችም በተሳታፊዎች ተጎብኝተዋል።
                            የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 4 people and indoor
May be an image of 9 people, people standing and indoor
May be an image of 14 people, people standing and indoor
May be an image of 11 people, people standing and indoor
May be an image of 1 person, sitting and standing
No photo description available.

KUE Hosts the First Joint International Conference

 
Kotebe University of Education (KUE) hosted the first joint international conference on ‘Education in Emergencies in East Africa: Implications for Sustainable Development’ in collaboration with the College of Education and Behavioural Studies, Addis Ababa University, and Ethiopian Construction Works Corporation.
In his opening remarks, Dr. Ebba Mijena, the Chief Executive Officer (CEO) of Higher Education Academic Affairs of the Ministry of Education of FDRE, emphasised that the productivity of the citizens and hence the development of the nation could be realised when the government and all stakeholders cooperatively invest in education. The CEO added that the joint conference is timely, and it could give the scholars opportunities to bring their expertise, practices and experiences together to enlighten the problems pertinent to education and come up with tangible solutions.
Dr. Tena Bekele, the KUE’s Vice President for Research and Community Service, remarked that the joint international conference was held with the aims of profiling the opportunities and challenges of intervening in the problems of the education sector and proposing policy directions in Ethiopia in particular and in East Africa in general.
Besides, Amenti Dadhi, the representative of the Ethiopian Construction Works Corporation, Prof. Darge Wole, the keynote speaker and Dr.Yekoyealem Dessie, the Conference Coordinating and Programming Committee Chairperson addressed the introductory and opening remarks to the audience.
In his closing remarks, having thanked the partners, event sponsors, organisers, and all the participants of the conference, Dr. Berhanemeskel Tena, the President, pointed out that KUE’s shift of focus from a metropolitan oriented-development mission to pure education was a breakthrough in the history of the higher education of Ethiopia. Dr Berhanemeskel further stipulated that the long-awaited ambition of having a world-class university of education that elevates the nation’s quality of education which is vividly driven by impactful research and development could only be fulfilled and sustained with combined efforts to be exerted by all passionate think tanks, professors, scholars, partners, and stakeholders.
It was evident that thirty-five papers (thirty-one research works and four keynote speeches prepared by invited writers) were presented at the conference both in the face-to-face and virtual modalities.
 
                       Communications Affairs Directorate
 
 
 
 
 
 
 
May be an image of 1 person
May be an image of 1 person and standing
May be an image of 1 person, standing and text that says
 
May be an image of 3 people, people standing and indoor
May be an image of 2 people, people sitting and indoorMay be an image of 5 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of one or more people, people standing and indoorMay be an image of 2 people, people standing, indoor and text that says
May be an image of 4 people, people standing and text that says
May be an image of 1 person, standing and indoor

ኮትዩ ለአንደኛ ዓመት ተማሪዎች የህይወት ክሂሎት ሥልጠና ሰጠ።

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ግንቦት 12/ 2014ዓ.ም የህይወት ክሂሎት ሥልጠና ያዘጋጀ ሲሆን፣ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ጊዜያዊ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሽመልስ ዘውዴ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ከቤተሰባቸው ርቀው ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ ዋና ዓላማቸው ትምህርት በመሆኑ፣ ይህንኑ ዓላማቸውን ከግብ ለማድረስ በጥንቃቄ መጓዝ አለባቸው ብለዋል።
የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ ዓላማቸውን ከሚያሰናክሉ ተግባራት መቆጠብ፣ በአልባሌ ሥፍራዎች እና ተግባራት ላይ አለመሳተፍ፣ የስነተዋልዶ ጤና ችግር የሚያስከትልባቸውን ጉዳት ቀድመው በማወቅ ጥንቃቄ ማድረግ፣ በትምህርታቸው ላይ ብቻ ትኩረት በማድረግ ውጤታማ ሆነው ለምርቃት እንዲበቁ እና ይህንንም ለማሳካት ሥልጠናው ጠቃሚ በመሆኑ፣ በትኩረት እንዲከታተሉ ዶ/ር ሽመልስ አሳስበዋል።
በሌላ በኩል የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አባይ በላይሁን የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲያችን በመጡበት ወቅት በተደረገላቸው አቀባበል አማካኝነት የቤተሰባዊነት ስሜት እና ጥሩ መቀራረብ መፈጠሩን አስታውሰው፣ አሁን የተዘጋጀው ሥልጠናም ተማሪዎቻችን በዩኒቨርሲቲው በሚቆዩባቸው ጊዜያት ማወቅ የሚገባቸውን ልዩ ልዩ የህይወት ክሂሎቶች በማስገንዘብ በኩል እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ፣ ሥልጠናውን በንቃት መከታተል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ምኞት ጌታቸው የስራ ክፍላቸው የስነተዋልዶ እና ተያያዥ ጉዳዮች ስልጠና እንዲሁም ኤች.አይ.ቪ/ ኤድስን በተመለከተ ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኙ ወገኖች አስፈላጊውን መረጃ እና አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
በሥልጠናው ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገልግሎቱን ያስተዋወቀ ሲሆን፣ የሥልጠናውን መርሐ ግብር መሠረት በማድረግ በግል እድገት (Personal Development)፣ በማህበራዊ ክሂሎት፣ በትምህርት ክሂሎት፣ በስነተዋልዶ ጤና እና ጎጂ ባህርያት ዙሪያ ለተማሪዎች ገለፃ ተደርጎ ውይይት ተካሂዷል።
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of one or more people, people sitting and indoor
May be an image of 1 person, standing and indoor
May be an image of 5 people, people sitting and indoor
May be an image of 5 people, people sitting and indoor
May be an image of 1 person, sitting, standing and indoor

FLH ORGANIZES TRAINING ON TEACHER PROFESSIONAL DEVELOPMENT

The Faculty of Languages and Humanities (FLH) of Kotebe University of Education offered a training titled “Teacher Professional Development: Implications for Quality of Education” to teachers on May 19, 2022.
Dr Fisseha Motuma, Dean of FLH, in his welcoming speech to the participants expressed that a major concern of an education university as Kotebe University of Education is improving teachers’ professional skills and competence on a sustainable basis. The Faculty has organized this training to support teachers by making them aware of the current professional improvement strategies, said Dr Fisseha.
Dr Girma Wossene, an Associate Professor in the Department of Foreign Languages and Literature, stressed the critically important roles that a comprehensive and sustainable professional development of teachers play in the quality of education during the training. Dr Girma also emphasized that both teachers and students can be competent in the 21st-century global market if their knowledge and professional development are up to the requirements of the modern information and communication technology, which constitutes the present-day education itself and the educational aids that are employed.
In his closing remarks, KUE’s Academic Affairs V/President, Dr Shimelis Zewdie, underpinned that all faculties, colleges and departments are expected to rethink and tune their working culture to the new approach as our University is improving and developing its structure as well as curriculum. Dr Shimelis expressed his appreciation for the faculty’s effort in acting within this frame of the University.
                                                       Communications Affairs Directorate
May be an image of 1 person
May be an image of 1 person
May be an image of 3 people, people sitting and indoor

KUE holds the 13th annual research symposium

Kotebe University of Education held its 13th Annual Research Symposium organized by the Research and Community Services V/President Office on May 16, 2022.
Dr Berhanemeskel Tena, the President of KUE, noted in his opening speech that instilling a research culture in a university plays a great role in the creation of knowledge as well as transferring it to the next generation. Underlining the highly interrelated relationship that exists between research and education (teaching), Dr Berhanemeskel opined that a good researcher could be a good teacher, implying the fact that engaging in research enhances the quality of education. Besides, the curriculum, which is being developed afresh in our university, aimed to produce a variety of experts in different disciplines by placing special emphasis on the quality of education, and our university is lucky as there are competent teachers who can translate this goal into reality, said the President.
KUE’s V/President for Research and Community Service, Dr Tena Bekele, on his part, pointed out that the primary purpose of a research symposium is enabling the staff to engage in academic dialogue and create a platform for their academic promotion as these exercises help them to establish an academic network with the conference participants.
Thirteen research works were presented in the symposium both in the morning and afternoon sessions.
                     Communications Affairs Directorate
May be an image of 1 person, standing and indoor
May be an image of 2 people and people sitting
May be an image of 4 people, people sitting, people standing and indoor

ኮትዩ ለአብርኆት ቤተ መጻሕፍት መጽሐፍትን በስጦታ አበረከተ።

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተቋቋመው ለአብርኆት ቤተ መጻሕፍት፣ መጽሐፍትን እንዲያሰባስብ ኃላፊነት በተሰጠው በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በኩል ግንቦት 2 ቀን 2014 ዓ.ም ከጉድለቱ ሦስት መቶ ሃምሳ አምስት መጻሕፍትን በስጦታ አበርክቷል።
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ስጦታውን በማስመልከት እንደተናገሩት፣ ተቋማችን ከሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የተውጣጡ በግምት ዋጋቸው ሰባት መቶ ሰባ ሺህ ብር የሚሆን ሦስት መቶ ሃምሳ አምስት መጻሕፍትን ለአብርኆት ቤተ መጻሕፍት በስጦታ ማበርከቱን ገልጸው፣ መጽሐፍት በትውልድ ቅብብሎሽ ለዘመናት ስለሚቆዩ ስጦታው ለትውልድ የተበረከተ እንደሆነ አድርጎ መውሰድ ይቻላል ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም አንባቢ ትውልድ ለመገንባት በሀገር ደረጃ በቂ ቤተ መጻሕፍት ሊኖሩ እንደሚገባ የገለጹ ሲሆን የተሠጡት መጽሐፍት ከአንደኛው ቤተመጽሐፍታችን ወደሁለተኛው ቤተመጽሐፍት እንደተሠጡ የሚቆጠር ነው ብለዋል። አያይዘው እንደገለፁት የሕዝባችንን አብሮነት እውን ለማድረግም የተማረ ትውልድ የመገንባትን አስፈላጊነት እንዲሁም ሃሳብን በጉልበት ከመሞገት ይልቅ በንባብ በታገዘ ዕውቀት መሞገት፣ ከስሜታዊነት ይልቅ የሰከነ ሕይወት ለመኖር እንደሚያስችል አብራርተዋል። የአብርኆት ቤተ መጻሕፍት እንደ ስሙ ሁሉ ትልቅ ሆኖ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲታወቅ ሁላችንም የድርሻችንን መወጣት እንደሚገባንና ለኅብረተሰባችንም እንዲህ ዓይነት ቤተ መጻሕፍቶችን በብዛት መገንባት እንደሚገባን ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል።
የዩኒቨርሲቲው የቤተ መጻሕፍትና አካዳሚክ ዶክመንቴሽን ዳይሬክተር አቶ ገብረመስቀል ግርማ የመጻሕፍት ስጦታውን በማስመልከት እንዳሉት፣ አብርኆት ቤተ መጻሕፍት ሁሉንም የማኅበረሰብ ክፍል ለማገልገል ተብሎ የተቋቋመ በመሆኑ የተቋማችን የቤተ መጻሕፍት ተጠቃሚዎች በስፋት የሚገለገሉባቸውን መጻሕፍት ለዚህ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት አካፍለናል ብለዋል። የተደረገው ስጦታም በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ካለን ላይ የማካፈል እና በጋራ የመቆምን አስፈላጊነት ያሳየ ከመሆኑም ባሻገር፣ የማኅበረሰቡን የአስተሳሰብ ደረጃ በመገንባት በኩል ሰፊ አስተዋፅኦ እንዳለውም አያይዘው ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የውጪ ቋንቋዎች ማኔጂንግ ኤዲተርና በተቋሙ ውስጥ በአሁኑ ሰዓት የአብርኆት ቤተ መጻሕፍት የመጽሐፍት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ በመሆን እየተጉ የሚገኙት አቶ ግዛቸው ደርብ ዩኒቨርሲቲው ለአብርሆት ቤተመጻሕፍት ላደረገው የመጻሕፍት አበርክቶ ከልብ አመስግነው፣ ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትም የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ፈለግ እንዲከተሉ ጠይቀዋል።
                                     የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of book

የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ የጀመረው ዕውቀትን የማጋራት መርሐ ግብር ለአካዳሚክ እውቀት ዕድገት ጠቃሚ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ።

ሚያዝያ 25/2014 ዓ.ም
የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ዕውቀትን የማጋራት መርሐ ግብሩን በ25/08/2014 ዓ.ም ባካሄደበት ወቅት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ጊ/ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሽመልስ ዘውዴ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር፣ ፋካልቲው የጀመረው እውቀትን የማጋራት መርሐ ግብር ለአካዳሚክ እውቀት ዕድገት ጠቃሚ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ እንቅስቃሴውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሰፋ እና የተለያዩ ተቋማትን እያሳተፈ መምጣቱን የጠቀሱት ዶክተር ሽመልስ፣ ለአካዳሚክ ዕውቀት እድገት በየጊዜው የሚደረግ አካዳሚያዊ የሆነ የውይይት መነሻ ሐሳብ መኖር ወሳኝ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እና የዕለቱ ዕውቀትን የማጋራት መርሐ ግብርም ስኬታማ እንዲሆን ያላቸውን መልካም ምኞት ገልፀዋል።
የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ዲን ዶ/ር ኃይለሚካኤል ሙሌ በበኩላቸው፣ ፋካልቲው በዕቅዱ መሠረት የምርምር ጉባኤ፣ የእውቀት ማጋራት መርሐ ግብሮችን፣ የቢዝነስ ዜና መጽሔት እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ተግባራትን በመምህራን እና በተማሪዎች አማካኝነት እያከናወነ ነው ብለዋል። የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ፈር ቀዳጅ በመሆን የጀመራቸውን ልዩ ልዩ ተግባራትንም አጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ዲኑ፣ የምርምር ሥራ ውጤት ለአካዳሚክ ማህበረሰብ ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ የህብረተሰቡን ችግር መፍታት እና በጥቅም ላይ መዋል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የፋካልቲው መምህር የሆኑት ዶክተር ያኪን አሊ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ የዋጋ ንረት በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ መፍትሔ የሚያሻው መሆኑን የገለፁ ሲሆን፣ መምህር ይልቃል ዋሴ ደግሞ የሀገሪቱ መዋቅራዊ ለውጥ ወደ አገልግሎት አሰጣጥ ያዘመመ በመሆኑ ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንፃር ውስንነት ስለሚኖረው የግብርና ምርት እና ምርታማነትን በመጨመር አገልግሎትን ማስፋት እና ወደ ፋብሪካ እና ኢንዱስትሪ መቀየር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በቀረቡት ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የውይይቱ መርሐ ግብር ሲጠናቀቅ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ዲን ዶ/ር ኃይለሚካኤል ሙሌ ፋካልቲው በቀጣይ ሀገር ዓቀፍ መድረክ ለማዘጋጀት ማቀዱንም አመልክተዋል።
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

10ኛው የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤት ቀን በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።

ሚያዚያ 28/2014 ዓ.ም
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 10ኛውን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤት ቀንን ባከበረበት ወቅት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ማቲማቲክስ ትምህርት (STEM Education) ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ፣ የበዓሉ ዋና ዓላማ 21ኛውን ክፍለ ዘመን የሚመጥን የሰው ኃይል በማፍራት የህብረተሰቡን ችግሮች በዘለቄታዊ ሁኔታ የሚቀርፉ የሳይንስ ውጤቶችን በተሻለ መንገድ ማቅረብ እንደሆነ ገልጸዋል። ዕለቱን በተማሪዎች መካከል ውድድር በመፍጠር ማክበርም ይህንን ዓላማ ከማሳኪያ መንገዶች አንዱ እና ዋነኛው መሆኑን አስገንዝበዋል።
በዚህም መሠረት በየካ ክፍለ ከተማ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን በማሳተፍ የፈጠራ ውጤታቸውን እንዲያቀርቡ በማድረግ፣ ዕለቱን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ማክበር እንደተቻለም አመልክተዋል። በዕለቱም በክፍለ ከተማው ከሚገኙ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ከሳይንስ ሼርድ ካምፓስ 39 ፕሮጀክቶች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራ እና በአይ.ሲ.ቲ ዘርፍ ቀርበው የተወዳደሩ ሲሆን፣ ለአሸናፊዎችም ሽልማት ተሰጥቷል።
በተማሪዎች የቀረቡት ፕሮጀክቶች ተስፋ ሰጪ በመሆናቸው ፕሮጀክቶቹ ጥቅም ላይ የሚውሉበትን መንገድ ማመቻቸት ከዩኒቨርሲቲው እና ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት የሚጠበቅ መሆኑንም ዶክተር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ አስገንዝበዋል።
                                                          የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

KUE Cohosts Capacity Building Workshop on Integrated Water, Sanitation and Hygiene for ONE HEALTH

Kotebe University of Education, with Bahir Dar University, hosted a three-day workshop aimed at training project participants on the application of Problem-Oriented Project-Based Learning (POPBL) and curriculum design as well as the development of the joint MSc program on IWS4ONEHEALTH as part of the project funded by NORPART—Norwegian Partnership Programme for Global Academic Cooperation on May 3, 2022, at Best Western Plus Hotel, Addis Ababa.
Dr Birhanemeskel Tena, the President of KUE, in his opening speech, thanked NORPART for funding the project which allows collaboration and partnership between the North partners (University of South-Eastern Norway, USN) and Norwegian University of Life Sciences, NMBU) and the South partners (Kotebe University of Education, Jimma, and Bahir Dar Universities) in staff exchange and student mobility. Dr Birhanemeskel also emphasized that KUE is the only education university in Ethiopia, and it contributes to the promotion of quality education as well as the internationalization of the study program which are components of the NORPART project. In addition, the President pointed out that he envisaged the collaboration between the North and South partner universities will be further developed and consolidated.
In the workshop, Dr Eshetu Janka, project coordinator at the University of South-Eastern Norway (USN), introduced the project and the new MSc program to the attendants, while Professor Sheri Bastien, a project participant from the Norwegian University of Life Sciences (NMBU), presented a lecture on the concept of WASH4ONEHEALTH. The presentations were followed by discussions based on questions and insights raised from the members of the project and participants from key stakeholders.
The seminar is expected to continue up to May 6 dwelling on issues pertinent to the project implementation and curriculum development for the joint MSc program and will be accompanied by a field visit to selected sites, such as Addis Ababa Waste Water Treatment Plant and Waste-to-Energy Facility. It is also understood that the project period is five years, and it ends in December 2026.
                            Communications Affairs Directorate

ማስታወቂያ

25/08/2014 ዓ.ም

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የተመዘገባችሁ ሁሉ የመግቢያ ፈተና ከሚያዝያ 29-30/2014 ዓ.ም ሲሆን የማመልከቻ ክፍያ 100 ብር ያልከፈላችሁ ከፈተናው ቀን በፊት በCBE 1000449424658 ከፍላችሁ ለፋይናንስ ክፍል ገቢ እንድታደርጉ እያሳሰብን የፈተናችሁ ፕሮግራም ከታች በተቀመጠው መሰረት መሆኑን እንገልፃለን::

ማሳሰቢያ: ተማሪዎች “Official transcript ” ከተመረቃችሁበት ዩኒቨርሲቲ ለማስላክ ዝግጅት ብታደርጉ።