ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የማስተማሪያ ቁስ ድጋፍ አደረገ

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያግዙ ቀለማቸው ነጭ እና አረንጓዴ የሆኑ ሃያ የማስተማሪያ ቦርዶችን ለኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ሚያዝያ 1 ቀን 2014 ዓ.ም በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት  አበርክቷል፡፡

ድጋፉን በቦታው በመገኘት ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር ያስረከቡት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ፤ ተቋማችን አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በተማሪዎች ቁጥር መጨመርና በሌሎች ምክንያቶች የመማሪያ ክፍል ጥበት ሲገጥመው ወደ ኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በመሄድ የመማር ማስተማሩን ተግባር እንደሚከውን ገልፀው፤ ዛሬ የተሰጠው ድጋፍም በትምህርት ቤቱ አመራርና በእኛ መምህራን በኩል የማስተማሪያ ቦርድ ችግር መኖሩ በተጠቆመው መሠረት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ቤቱ ጋር ባለው መልካም ግንኙነት እና ከቅርበቱም የተነሳ እስካሁን ድረስ በጋራ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን፤ በቀጣይም ትምህርት ቤቱን እንደሞዴል በመውሰድ የተለያዩ የማኅበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን እንደሚያከናውን ተናግረዋል፡፡

የኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርት የሆኑት ወ/ሮ ዓለም አበበ ድጋፉን በተረከቡበት ወቅት እንዳሉት፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ጥቁር ሰሌዳዎቻችን እጅግ በመበላሸታቸው ምክንያት የመማር ማስተማሩን ተግባር ለመከወን ችግር እንደነበረባቸው አውስተው፤ አሁን ግን በቅርበት የሚገኘው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተለዩና አዳዲስ የማስተማሪያ ሰሌዳዎችን በስጦታ ስላበረከተልን የገጠመን የጥቁር ሰሌዳ ችግር ሙሉ ለሙሉ ተወግዶልናል ብለዋል። በመቀጠልም  ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ የምርምርና የማማከር ሥራዎችን በትምህርት ቤቱ እያከናወነ እንደሆነ የገለጹት ርዕሰ መምህርቷ፤ በቀጣይም በተቋማችን ውስጥ የሚስተዋሉ ለተማሪዎች መመገቢያ የሚሆኑ ወንበሮች፣ ያገለገሉ ኮምፒውተሮችና የሌሎችም ቁሳቁሶች ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት የሥራ ስነ-ምግባርና ተቋማዊ ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረ ስልጠና አካሄደ፡፡

የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት “በትምህርት ተቋማት የሥራ ስነ-ምግባርና ተቋማዊ ባህል ግንባታ” በሚል ርዕስ ለአስተዳደር ሠራተኞችና ለአመራሮች ከስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ ትምህርት ክፍል በተጋበዙ መምህራን መጋቢት 28 እና 29/2014 ዓ.ም ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያሰሙት የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ነጋሽ፣ በስነ-ምግባርና በተቋማዊ ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረው ስልጠና ሠራተኞችም ሆኑ ፈፃሚ አካላት ህግና ደንብን ተከትለው ለህዝብና ለሀገር ጥቅም መስራት የሚገባቸውን ስራዎች በአግባቡ ለመስራት የሚያስችላቸውን ግንዛቤ ያስጨብጣቸዋል ብለዋል፡፡ ስልጠናው በሠራተኛውም ሆነ በዩኒቨርሲቲው አመራሮች ዘንድ የስነ-ምግባርና የተቋማዊ ባህል ግንባታ ግንዛቤ ከማስጨበጡም በተጨማሪ፣ ሥራን በጥራትና በፍጥነት በመስራት ረገድ ከአስተሳሰብ ጀምሮ ተቋማዊ ለውጥ እስከማምጣት የሚደርስ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመናል ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ ትምህርት ክፍል መምህርት የሆኑት ወ/ሮ ገነት አበበ በዚሁ ጊዜ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ጽሑፍ የስልጠናው ዋና ዓላማ የሥራ ሥነ-ምግባር፣ የመልካም አስተዳደር፣ የተቋማዊ ባህል እና ሞራላዊ ምክንያታዊነት እንዲሁም የሥራ ውጤታማነት በትምህርት ተቋማት ውስጥ ማስገንዘብ መሆኑን ጠቁመው፣ ከስልጠናው በኋላም ሃላፊነትን የማወቅና በአግባቡ የመወጣት፣ የሥራ ተነሳሽነትና የዩኒቨርሲቲውን የሥራ ባህል እንደገና በመቃኘት ሰልጣኞች ጥሩ የሥራ ባህል እንዲያዳብሩ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል። የሥራ ላይ ስነ-ምግባር መርሆዎች ቅንነት፣ ታማኝነት፣ ግልፅነት፣ ተጠያቂነት፣ ሀቀኝነት፣ ምስጢር መጠበቅ፣ አለማዳላት እና ህግን ማክበር መሆናቸውን የዘረዘሩት መምህርቷ፣ የተቋሙ ድክመትም ሆነ ጥንካሬ የጋራ በመሆኑ፣ ተቋማዊ ባህል ለመገንባት ሁለገብ ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል።
ስልጠናው በሁለት ምድብ የተከፈለ ሲሆን፣ በሁለተኛው ዙርም የስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት አቶ እያሱ በሬንቶ የትምህርታዊ ውይይት መነሻ ሃሳብ አቅርበው በሰራተኞቹና በአመራሮቹ ተመሳሳይ ውይይት ተካሂዷል።
                                                               የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መምህራን አስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች በሙሉ

የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በዩኒቨርሲቲው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ መጽሔት በቅርቡ ለማሳተም በዝግጅት ላይ ይገኛ፡፡ስለሆነም ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ማንኛውም ልዩ ልዩ መጣጥፎች፣ለግንዛቤ የሚሆኑ መልዕክቶችን እና ግጥሞችን ወዘተ. አዲሱ የአስተዳደር ህንፃ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 10 ወይም በቴሌግራም https://t.me/sileshics እስከ መጋቢት 30/2014 ዓ.ም ለክፍሉ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

                   የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

                 27/07/2014 ዓ.ም

Relevance and Quality Assurance Directorate Organizes Training to KUE’s Academic Leaders

The Relevance and Quality Assurance Directorate of Kotebe University of Education organized a one-day training under the theme “Education Quality and Institutional Governance Nexus” for the KUE Academic leaders to help them play significant roles in ensuring the quality of education.
Honourable Dr. Birhanemeskel Tena, the President of KUE, stressed in his opening speech that the present training is unique in its kind as the issue of education quality touches everyone and every activity in the Institution. Dr. Birhanemeskel also underlined the fact that quality in education is ensured using a range of parameters and of these having teachers with professional integrity, placing priority on students as well as developing a knowledge-led system are the major ones. The President further emphasized the role of teachers in bringing quality education and creating capable citizens in a country.
Two experts from the Education and Training Authority (ETA), namely Mr.Sisay Tekle, Quality Audit, and Enhancement Senior Expert, and Dr. Dunkana Negussa, Director of Quality Audit & Enhancement Directorate, delivered their expertise-based knowledge on the topics:‘Quality in Higher Education and Governance (Leadership)’ and quality Nexus’ respectively. The presentations were followed by discussions based on questions, opinions, and views raised by the participants.
In his closing speech, Dr. Shimelis Zewdie, Academic Affairs V/President, KUE, highlighted the importance of viewing quality in higher education from three perspectives: quality in the learning-teaching process, in research, and publications as well as in basic infrastructure, which is a precursor for the first two. Adding to that, Dr. Shimelis called upon the leaders at KUE to mobilize resources, coordinate the personnel and create a system of monitoring and evaluation so as to bring about quality in the institution.
Communication Affairs Directorate
April,01,2022

KUE’s Sport Science Academy Holds a Symposium

A Symposium that conferred the impact of ‘Physical Education, Sport and Exercise o n the Growth and Development of a Healthy Lifestyle’ was held by the Sports Science Academy of  Kotebe University of Education on March 29, 2022, in the presence of academic staff, students, and alumni.
In his opening speech, Dr. Shimelis Zewdie, Academic Affairs V/President, Kotebe University of Education, reminded the audience that Kotebe as an academic institution has been branded in the enterprise of its Sport Science Academy, the then Department of Health and Physical Education. He also expressed that the present platform is an opportunity to raise the standard of the University. As to Dr. Shimelis, sport contributes to the growth of a country for it physically and mentally nurtures manpower who is central to any development endeavors.
Three papers, “The Long Journey of Sport Science Academy in the History of KUE”, “Age is not a Limiting …” and “Physical Exercise for Leadership, Health and Effectiveness” by Dr. Yemane Gossaye, Mr. Muluneh Girma and Mr. Netsanet Kassa (an alumnus of KUE) respectively, were presented and discussed in the event. The paper presentations were accompanied by aerobic and other physical exercises orchestrated by renowned aerobic and fitness team members who themselves were led by the alumni of the University.
In the event, a book titled “የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጤናማ ህይወት” written by Dr. Tilahun Bereded was inaugurated. Individuals and institutions who contributed to the realization of the symposium were also given certificates of recognition.
In his closing remark, Dr. Yemane Gossaye, the Director of Sport Science Academy, noted that the Academy has plans to launch new academic programs, which give community service and entertain symposia that involve a range of stakeholders and alumni.
                                                   Communication Affairs Directorate

Kotebe University Education signs memorandum of understanding with University of South-Eastern Norway

Kotebe University of Education and the University of South-Eastern Norway have signed a memorandum of understanding to jointly work on a project named Capacity Building in Integrated Water, Sanitation and Hygiene for ONE HEALTH on a long-term basis to foster academic cooperation, mobility of students as well as staff, and research collaboration in a meeting held virtually on March 11, 2022.

In his opening speech in the project kick-off meeting conducted virtually, Dr Tesfaye Negash, Vice President for Administration and Student Service, Kotebe University of Education, underlined the importance of the project in enhancing the quality of education in higher education and thanked NORPART-Norwegian Partnership Programme for Global Academic Cooperation for funding it. He also appreciated the agreement as it happened in the advent that our university became a university of education (KUE). Moreover, Dr Tesfaye promised the participants to facilitate administrative matters pertinent to the project that come under his jurisdiction.

Thor-Egil Elide, the project administrator, on his part, noted that the project seeks to ensure the quality and internationalization of higher education in Norway and selected partner universities from developing countries through academic cooperation and mutual student mobility.

It is understood that the partnership agreement involves Jimma and Bahir Dar Universities in addition to Kotebe University of Education and stays in effect for the next five years.

 Communication Affairs Directorate

 

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ፤ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከዚህ በታች በተጠቀሱት ፕሮግራሞች የግል
(
Tuition Fee-Paying Study Applicant’s) በመደበኛ ፕሮግራም (ጀነሪክ እና ፖስት ቤዚክ) እና በድህረ ምረቃ ፕሮግራም በመደበኛ
እና በእረፍት ቀናት በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ትምህርታቸውን መከታተል የሚፈልጉ አመልካቾችን ተቀብሎ ለማስተማር
ዝግጅት ያጠናቀቀ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው፡፡
አመልካቾች የሚከተሉትን የቅበላ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
1. የመሰናዶ ትምህርት ያጠናቀቁ እና ቅድመ-ምዝገባ ወቅት የትምህርት ሚንስቴር ለትምህርት ዘመኑ ያሳወቀውን የመቁረጫ
ነጥብ ማሟላታቸው፤ የተረጋገጠ እና ማሟላት የሚችሉ፤ [ለ አራት አመት ፕሮግራም (Generic Program].
2. ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም የተመረቁ የጤና ባለሙያዎች ከሰለጠኑበት የሙያ መስክ ጋር በአዲሱ
የትምህርት ፖሊሲ በደረጃ 4 ወይንም በቀድሞው 10+3 ወይንም 12+2) ያጠናቀቁ ሆነው በሙያው ደረጃ 4 የብቃት
ማረጋገጫ ምዘና (COC level 4) ተፈትነው ያለፉበትን፤ እንዲሁም በሙያው ቢያንስ የአንድ ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው
መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች በድጋሜ-ምዝገባ እለት ማቅረብ የሚችሉ፤ [ለ ፖስት ቤዚክ ፕሮግራም (Post Basic
Program) ].
3. ከውጭ ሃገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃ ያላቸው አመልካቾች ከሆኑ፤ ከኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የአቻ
ግምት አሰርተው፤ ለመጀመሪያ ዲግሪ ማመልከት ያሚያስችል ማስረጃ በድጋሜ-ምዝገባ እለት ማቅረብ የሚችሉ፤

4. ለድጋሜ-ምዝገባ የተመዘገቡ አመልካቾች በኮሌጁ የሚዘጋጁትን የመግቢያ ፈተናዎች መውሰድ እና ማለፍ የሚጠበቅባቸው
ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ
በቅድመ-ምዝጋባ ወቅት ምንም አይነት የማመልከቻ ክፍያ የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡
ዳግም-ምዝገባ የሚከናወነው፤ የ2014ዓ.ም የ 12ኛ ክፍል ትምህርት ሚንስቴር ለትምህርት ዘመኑ ያሳወቀውን የማለፊያ
ነጥብ ከተገለጸ በኋላ በኮሌጁ በአካል በመገኘት ይሆናል፡፡
እጩ አመልካቾች በኮሌጁ የሚሰጡ መደበኛ ፕሮግራም የጀነሪክ እና ፖስት ቤዚክ መደበኛ ፕሮግራሞችን ፤ ከታች
ከተያያዘው የጎግል ፎርም ሊንክ ገብተው ማየት ይችላሉ፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ እጩ አመልካቾች፤ከታች የተጠቀመጠውን የማመልከቻውን ማስፈንጠሪያ(
link) ተጠቅመው ቅድመ ምዝገባ ማከናወን የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ለበለጠ መረጃ ከዩኒቨርሲቲው ድህረ-ገጽ http://www.kmu.edu.et, Facebook ገጽ:
https://www.facebook.com/ww.kmu.edu.et ፣ በኮሌጁ ኢሜል አድራሻ: meneilk.hsc@kmu.edu.et ፣ከኮሌጁ
ተማሪዎች ቴሌግራም ገጽ፡ KUE Menellik Medical & Health Science College Student’s channel (link:
https://t.me/kmumhsc በተጨማሪም ከ”ዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሠራተኞች” ቴሌግራም ገጽ
ማግኘት ይችላሉ፡፡
[Access the Online Application Form] https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfwoA2iMYqKoSSPWzK6vR5K45GGEELZaL9fL5m6TMB4xV9-4Q/viewform
[Access the online Downloadable Application Form] https://docs.google.com/document/d/1GSJ2_24BiLq8SMYVsrTGKUVtX5zps-jRiFCA0JX5Rk8/edit?usp=sharing
የቅድመ-ምዝገባ ማመልከቻ ጊዜ ከመጋቢት 01-07-2014ዓ.ም እስከ መጋቢት 10-07-2014 ዓ.ም 12፡00 ሰዓት ብቻ
ማመልከቻ የምንቀበል ይሆናል፡፡
ለግንዛቤ
በጤና ሚኒስቴር የጤና ባለሙያዎቸ ብቃት ምዘናና ፈቃድ ዳይሬክቶሬት በሚሰጠው የብቃት ምዘና ፤የኮሌጁ ተማሪዎች
በአማካኝ መጠነ-ማለፍ
(Pass Rate) ከ 95% በላይ ፤ ያስመዘገበ መሆኑ፤ ተቋሙን ተመራጭ ያደርገዋል፡፡
ኮሌጁ ማሀበረሰቡን ማገልገል አላማው በመሆኑ፤ ከተማሪዎችና ወላጆች የሚጠይቀው ከመማር ማስተማር ወጪ ውስጥ የትምህርት
ወጪ ብቻ መሆኑ፤
ዋና ዋና የትምህርት ክፍያዎች በቀጣይ በተቀመጠው ሰንጠረዥ መሰረት ይሆናሉ፡፡


ተ.ቁ የክፍያ አይነት የክፍያ ተመን
1. የማመልከቻ ክፍያ (በመልሶ ምዝገባ) 100
2. የትምህርት ክፍያ በክሬዲት ለቲዎሪ አወር 95
3. ለሰርቶ ማሳያ፣ ተግባር ልምምድ በክሬዲት አወር 63.33

በኮሌጁ የሚሰጡ ፕሮግራሞች ዝርዝር

S.NO LIST OF DEPARTMENT MODALITY DURATION OF STUDY /YEAR
1 Nursing Generic 4
Post basic 2/1/2
2 Medical Laboratory Science Generic 4
Post basic 2/1/2
3 Medical Radiology Technology Generic 4
Post basic 2/1/2
4 Pharmacy Generic 5
Post Basic 3
5 Psychiatry Nursing Generic 4
Post Basic 2/1/2
6 Midwifery Generic 4
Post Basic 2/1/2

 

7 Human Nutrition Generic 4
8 Health Informatics Post Basic 2/1/2
9 Family Health Post basic 2/1/2
10 Emergency and Critical Care Nursing Post basic 2/1/2
11 Surgical Nursing Post basic 2/1/2
12 Pediatrics and Child Health Nursing Post basic 2/1/2
13 Neonatal Nursing Post basic 2/1/2
14 Operative Theater Nursing Post basic 2/1/2
15 Anesthesia

Post basic

Generic

3

4

 

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ፤ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከዚህ በታች በተጠቀሱት ፕሮግራሞች የግል (Tuition
Fee-Paying Study Applicant’s
) በመደበኛ ፕሮግራም (Regular እና እረፍት ቀናት (Weekend) በ2014ዓ.ም የትምህርት ዘመን
ትምህርታቸውን መከታተል የሚፈልጉ አመልካቾችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት ያጠናቀቀ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው፡፡
አመልካቾች የሚከተሉትን የቅበላ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
1. እውቅና ካለው ተቋም በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁና ከሚያመለክቱበት የትምህርት መስክ ጋር ዝምድና ያለው የት/ት ዝግጅት
ያላቸው፤
2. ከውጭ ሃገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃ ከሆነ፤ ከኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የአቻ ግምት አሰርተው፤ ለሁለተኛ
ዲግሪ ማመልከት የሚያስችል ማስረጃ በድጋሜ-ምዝገባ እለት ማቅረብ የሚችሉ፤
3. ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ከድጋሜ ምዝገባ በኋላ ማቅረብ የሚችሉ፤
ማሳሰቢያ
በቅድመ-ምዝገባ ወቅት ምንም አይነት የማመልከቻ ክፍያ የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ዳግም-ምዝገባ እና የመግቢያ ፈተና ጊዜ በማስታወቂያ ሰሌዳ ወይንም በሌሎች የተግባቦት ዘዴዎች የሚገለጽ ሆኖ አመልካቹ/ቿ
በኮሌጁ በአካል መገኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡
ለድጋሜ-ምዝገባ የተመዘገቡ አመልካቾች በኮሌጁ የሚዘጋጁትን የመግቢያ ፈተናዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡
እጩ አመልካቾች በኮሌጁ የሚሰጡ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም የመደበኛ (Regular) እና እረፍት ቀናት(Weekend)
ፕሮግራሞችን፤ ከታች ከተያያዘው Online Link ገብተው መመልከት ይችላሉ፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ እጩ አመልካቾች፤ከታች የተጠቀመጠውን የማመልከቻውን ማስፈንጠሪያ( link)
ተጠቅመው ቅድመ-ምዝገባ ማከናወን የሚችሉ እና ተጨማሪ የመመዝግቢያ ፎርም ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
2
ለበለጠ መረጃ ከዩኒቨርሲቲው ድህረ-ገጽ http://www.kmu.edu.et, Facebook ገጽ: https://www.facebook.com/ww.kmu.edu.et
፣ በኮሌጁ ኢሜል አድራሻ: meneilk.hsc@kmu.edu.et ፣ከኮሌጁ ተማሪዎች ቴሌግራም ገጽ፡ KUE Menellik Medical & Health
Science College Student’s channel (link:
https://t.me/kmumhsc በተጨማሪም ከ”ዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ
ኮሌጅ ሠራተኞች” ቴሌግራም ገጽ ማግኘት ይችላሉ፡፡
[Access the Online Application Form] https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSczyp-S1h0SFdCcS_qugwS64g3isnhQ3CwKpqiaaZacB65wtA/viewform
[Access the online Downloadable Application Form] https://docs.google.com/document/d/1k1n2SB_QynGG5fLVp3becrBxsCD4ZvuUnDfFRNH1p0o/edit?usp=sharing
የቅድመ-ምዝገባ ማመልከቻ ጊዜ ከመጋቢት 01-07-2014ዓ.ም እስከ መጋቢት 10-07-2014 ዓ.ም 12፡00 ሰዓት ብቻ ማመልከቻ
የምንቀበል ይሆናል፡፡
የትምህርት ክፍያዎች በቀጣይ በተቀመጠው ሰንጠረዥ መሰረት ይሆናሉ፡፡

ተ.ቁ የክፍያ አይነት የክፍያ ተመን /በብር
1. የማመልከቻ ክፍያ (በመልሶ ምዝገባ) 100
2. የትምህርት ክፍያ በክሬዲት አወር 900
3. የምርምር ክፍያ 10,000

በኮሌጁ የሚሰጡ ፕሮግራሞች ዝርዝር

S.No List of Department Modality Duration Of Study /Year
1 Public Health Nutrition Regular
Weekend
2
3


2 Health Service Management Regular
Weekend     
2
3
                                                                                                                  

ታላቁ የህዳሴ ግድባችን የድህነት ማሸነፊያ ተስፋችን መሆኑ ተገለጸ

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ፕሮጀከት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወቅታዊ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ የውይይት መርሐ-ግብር በ26/06/2014 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ አስተናግዷል።
ውይይቱ በተጀመረበት ወቅት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያሰሙት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የተከበሩ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና፣ የህዳሴው ግድብ የድህነት ማሸነፊያ ተስፋችን መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በመቀጠልም ፕሬዝዳንቱ ግድቡ የይቻላል አቅም መገንቢያችን በመሆኑ ወጣቱ ትውልድ የህዳሴው ግድብ አምባሳደሮች በመሆን ለዓለም ህዝብ ስለህዳሴው ግድብ መመስከር እና በየዕለቱም መናገር ብሎም በቀጣይነት ድጋፉን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከሚመገቡት ምግብ በመቀነስ ለህዳሴው ግድብ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ሲያበረክቱ መቆየታቸውን ያስታወሱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት፣ በቀጣይም ከድህነት እና ከጨለማ ውስጥ የመውጣት አስተሳሰብ በማጎልበት በእውቀታችን፣ በገንዘባችንና በጉልበታችን አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ተወካይ የሆኑት ዶክተር ታምራት ይገዙ በበኩላቸው ትምህርት ከድህነት ለመውጣት ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ መንግሥት ለትምህርት ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራ የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በእውቀት የታነፀ እና ሀገርን ከድህነት ለማውጣት ቁርጠኛ የሆነ ትውልድ ለማፍራት በተለይ የወጣቱ ትውልድ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ወጣቱ ትውልድ ባለፉት ዓመታት ለህዳሴው ግድብ መሳካት ቦንድ በመግዛት ያሳየው የነቃ ተሳትፎ ለሀገሩ እድገት የሚቆረቆር ዜጋ እያፈራን ስለመሆኑ ምስክር ነው በማለትም ተናግረዋል፡፡
በዕለቱም ለውይይት መነሻ የሚሆኑ ሦስት ጽሑፎች ቀርበው በተማሪዎቹ ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን፣ ተማሪዎች በህዳሴው ግድብ ዙሪያ እውቀት፣ አስተሳሰብና አመለካከትን በአግባቡ በመቅረፅ እና በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች በማስረዳትና በማስተዋወቅ፣ አፍራሽ አመለካከቶችን በመመከት እንዲሁም ትክክለኛውን መረጃ በመስጠት የአምባሳደርነት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ተብሏል፡፡ ተማሪዎችም በበኩላቸው የራሳቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልጸዋል፡፡
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ፕሮጀከት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሄ ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር የተደረገው ውይይት ውጤታማ እንደነበር ጠቅሰው ተማሪዎችም ሀገሪቱን ከጨለማ ወደ ብርሃን ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት የእስካሁኑን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡
                               የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት