የ2014 ዓ.ም የ2ኛ ድግሪ ትምህርትን በተመለከተ

በ2014 ዓ.ም ዩኒቨርስቲያችን ከሜትሮፖሊታን ወደ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ መቀየሩን ተከትሎ የ2014 ዓ.ም ምዝገባ መተላለፉ ይታወቃል። በመሆኑም አዳዲስ የ2ኛ ድግሪ ፕሮግራሞች በ”Masters of Education” በቅርቡ ምዝገባ ለመጀመር ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን እየገለጽን፣ ቀደም ብሎ ምዝገባ የተካሄደባቸው የ2ኛ ድግሪ ፕሮግራሞች ምዝገባው በ”Online” እስከ ሚያዝያ 18/2014 ዓ.ም መቀጠሉን እናሳውቃለን።
ማሳሳቢያ: ከዚህ በፊት በ”Online” ለተመዘገባችሁ ለምዝገባ የከፈላችሁት ብር ታሳቢ የምናደርግ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
– ለፕሮግራሞቹን ዝርዝርና የማመልከቻ ሊንክ/የሚቀጥለውን ማስፈንጠርያ ይጫኑ::
– ለበለጠ መረጃ: +251118723289 ወይም
– የየኮሌጅ ሬጂስትራር በአካል በመገኘት ይጠይቁ።
                                                                                               የድህረ ምረቃ ት/ቤት

ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ የሚያዘጋጀው የእውቀት ማጋራት መርሐ ግብር መጠናከርና በሌሎች መለመድ እንዳለበት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ገለፁ።

የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ሦስተኛውን የእውቀት ማጋራት መርሐ-ግብር በ11/08/2014ዓ.ም ባካሄደበት ወቅት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና፣ ፋካልቲው የሚያዘጋጀው ወርሃዊ የእውቀት ማጋራት መርሐ-ግብር እንደጥሩ ልምድ ተወስዶ ከዚህ የበለጠ በሀገር ዓቀፍ ደረጃ ማደግ እና መስፋት እንዳለበት ገልፀዋል። ተማሪዎችም እውቀት የሚቀስሙበት በመሆኑ ልምዱ በሁሉም ፋካልቲዎች መለመድ አለበት ብለዋል።
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሽመልሽ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ፈር ቀዳጅ ሆኖ ብዙ ጥናታዊ ጽሑፎችን እና መድረኮችን በተከታታይ በማዘጋጀት በግንባር ቀደምትነት የሚተጋ ፋካልቲ በመሆኑ ለማመስገን እወዳለሁ ካሉ በኋላ፣ የዛሬው ውይይት ዓለም ዓቀፋዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተዘጋጀ እንደመሆኑ መጠን ውይይቱን አስፈላጊና የተለየ እውቀት የሚገኝበት ነው ሲሉ ተናግረዋል። ይህ ዓይነቱን እውቀት የማጋራት መድረክ የተወሰኑት ፋካልቲዎች የጀመሩ ቢሆንም የተቀሩት ፋካልቲዎች ከዚህ አይነቱ መድረክ ተምረው ብዙ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
የቢ.ኢ.ፋ ዲን የሆኑት ዶ/ር ኃይለሚካኤል ሙሌ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ባሰሙበት ወቅት፣ በፋካልቲያችን ደረጃ አቅደን ከምንሰራቸው ሥራዎች ውስጥ አንዱ ይህ የእውቀት ማጋራት ሲሆን፣ በቀጣይ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎትን የተመለከቱ ሁለት መድረኮች በተከታታይ እንደሚቀርቡና የኒውስሌተር ዝግጅትም እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ጉዳይ በአብዛኛው የጋራ ጉዳይ በመሆኑ፣ ሰፋ ባለ መድረክ የሚያወያዩ ሀገራዊ እና ዓለምዓቀፋዊ አጀንዳዎችን በመቅረፅ እንደሚቀርቡ አሳውቀዋል።
በመርሐ-ግብሩ ላይ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ እንዲሁም የሩሲያና የዩክሬን ጦርነት በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ያስከተሉትን ተፅዕኖ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከቱ ሁለት የውይይት መነሻ ጽሑፎች የፋካልቲው መምህራን በሆኑት በአቶ ዮናስ አብርሃ እና በአቶ አብደላ ቆሳ ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
                                                           የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

KUE Confers with Scholars and High-level Leaders upon Its Transitional Roadmap

April 16, 2022
Kotebe University of Education had a high-level consultative meeting with a panel of scholars, and high-level ministerial and managerial leaders on its transitional roadmap. The participants of the panel discussion consisted of a state minister, renowned education professors and KUE’s Board, management and technical team, and steering committees coordinators.
At the outset of the meeting, Honourable Dr. Berhanemeskel Tena, the President of the University, and Dr. Samuel Kefle, the State Minister, delivered the welcome speech, and opening remarks respectively. Dr. Fekede Tuli, the technical team leader, also gave a brief introduction to the transitional roadmap. Following that, four scholars, namely Prof. Yalew Endawoke, Prof. Belay Tefera, Dr. Wondweson Tamirat, and Dr. Meskerem Lechisa reviewed the roadmap document and presented their unreserved enlightenment on it at the event. The technical team coordinators also had the opportunity to reflect on the points made by the reviewers of the transitional roadmap document.
In addition to the professors who presented their views at the forum today, the President said other high-level academic experts also took the document and reviewed it, and once the document has been properly developed, it will be presented to stakeholders at a broader stage.
Eventually, Ato Abadula Gemeda, the KUE’s Executive Board Chairperson, remarked that Kotebe has to fully exploit the expertise of the scholars to bring change in the quality of education that is desired to happen in the nation.
It is well recalled that Kotebe rebrands itself from a metropolitan-oriented institution to an education university.
                                                          Communication Affairs Directorate

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መላው አመራሮች በዩኒቨርሲቲው ፍኖተ-ካርታ እና አጠቃላይ የመምህራን ማህበር ማቋቋሚያ ላይ መከሩ

(ማክሰኞ 27/07/2014)

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት በተከበሩ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና ሰብሳቢነት በዩኒቨርሲቲው ፍኖተ-ካርታ ላይ በሠፊው መክረው በሂደቱም ላይ የነበረው ምቹ ሁኔታ እና ተግዳሮቶች ውይይት ተደርጎባቸው መግባባት የተደረሰባቸው ሲሆን፣ ሰነዱ በተሠጠው ግብዓት ዳብሮ ለውሳኔ ለትምህርት ሚኒስቴር እንዲቀርብ ሆኗል።
በሌላ በኩል ዩኒቨርሲቲው የመምህራን ማህበር ለማቋቋም የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ የመነሻ ሀሳቡ በጊ/የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ ቀርቦ የመምረጫ ጊዜ ሠሌዳ ተቀምጦ ስብሰባው ተጠናቋል።
                                       የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የአፈፃፀም መመሪያ ላይ ተወያየ።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች የትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አፈፃፀም መመሪያ ዙሪያ ላይ መጋቢት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ውይይት አካሄዱ።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሽመልስ ዘውዴ ለውይይቱ የመነሻ ሃሳብ ባቀረቡበት ወቅት፣ ለመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች የተዘጋጀው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን በዩኒቨርሲቲዎች መካከልም የተወዳዳሪነትን መንፈስ ያጎለብታል ብለዋል፡፡ ዶክተር ሽመልስ በመቀጠልም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሩቃን ገበያው የሚፈልገውን አቅምና ብቃት ያሟሉ መሆናቸውን በፈተና መፈተሽ አስፈላጊ በመሆኑ፣ ይህ የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አሰጣጥ መመሪያ መዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡

የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የተከበሩ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና በዚሁ ጊዜ በሰጡት አስተያየት የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አሰጣጥ መመሪያው ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራንና ተቋማትም ተወዳዳሪ እና ብቁ ሆነው የሚገኙበትን አሰራር ስለሚፈጥር፣ ለአተገባበሩ ልዩ ትኩረት መስጠትና በዩኒቨርሲቲያችን ደረጃም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡

በመመሪያው ላይ በተደረገው ውይይት ተሳታፊ የነበሩት መምህራንም የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አሰጣጥ መመሪያውን ከመተግበር ባሻገር ሥርዓተ ትምህርቱን ማሻሻል፣ የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላና የትምህርት አሰጣጥ መርሐ-ግብርን ማስተካከል፣ ለትምህርት ጥራት የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ማሟላት፣ ጊዜው አጭር እና ውሳኔውም የፈጠነ በመሆኑ፣ መመሪያውን የሚያስፈፅም ራሱን የቻለ ጽሕፈት ቤት በዩኒቨርሲቲያችን ደረጃ ማቋቋም አስፈላጊ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የማስተማሪያ ቁስ ድጋፍ አደረገ

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደትን የሚያግዙ ቀለማቸው ነጭ እና አረንጓዴ የሆኑ ሃያ የማስተማሪያ ቦርዶችን ለኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ሚያዝያ 1 ቀን 2014 ዓ.ም በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት  አበርክቷል፡፡

ድጋፉን በቦታው በመገኘት ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር ያስረከቡት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ፤ ተቋማችን አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በተማሪዎች ቁጥር መጨመርና በሌሎች ምክንያቶች የመማሪያ ክፍል ጥበት ሲገጥመው ወደ ኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በመሄድ የመማር ማስተማሩን ተግባር እንደሚከውን ገልፀው፤ ዛሬ የተሰጠው ድጋፍም በትምህርት ቤቱ አመራርና በእኛ መምህራን በኩል የማስተማሪያ ቦርድ ችግር መኖሩ በተጠቆመው መሠረት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ቤቱ ጋር ባለው መልካም ግንኙነት እና ከቅርበቱም የተነሳ እስካሁን ድረስ በጋራ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን፤ በቀጣይም ትምህርት ቤቱን እንደሞዴል በመውሰድ የተለያዩ የማኅበረሰብ አገልግሎት ስራዎችን እንደሚያከናውን ተናግረዋል፡፡

የኮተቤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርት የሆኑት ወ/ሮ ዓለም አበበ ድጋፉን በተረከቡበት ወቅት እንዳሉት፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ጥቁር ሰሌዳዎቻችን እጅግ በመበላሸታቸው ምክንያት የመማር ማስተማሩን ተግባር ለመከወን ችግር እንደነበረባቸው አውስተው፤ አሁን ግን በቅርበት የሚገኘው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተለዩና አዳዲስ የማስተማሪያ ሰሌዳዎችን በስጦታ ስላበረከተልን የገጠመን የጥቁር ሰሌዳ ችግር ሙሉ ለሙሉ ተወግዶልናል ብለዋል። በመቀጠልም  ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ የምርምርና የማማከር ሥራዎችን በትምህርት ቤቱ እያከናወነ እንደሆነ የገለጹት ርዕሰ መምህርቷ፤ በቀጣይም በተቋማችን ውስጥ የሚስተዋሉ ለተማሪዎች መመገቢያ የሚሆኑ ወንበሮች፣ ያገለገሉ ኮምፒውተሮችና የሌሎችም ቁሳቁሶች ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት የሥራ ስነ-ምግባርና ተቋማዊ ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረ ስልጠና አካሄደ፡፡

የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት “በትምህርት ተቋማት የሥራ ስነ-ምግባርና ተቋማዊ ባህል ግንባታ” በሚል ርዕስ ለአስተዳደር ሠራተኞችና ለአመራሮች ከስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ ትምህርት ክፍል በተጋበዙ መምህራን መጋቢት 28 እና 29/2014 ዓ.ም ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያሰሙት የአስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ነጋሽ፣ በስነ-ምግባርና በተቋማዊ ባህል ግንባታ ላይ ያተኮረው ስልጠና ሠራተኞችም ሆኑ ፈፃሚ አካላት ህግና ደንብን ተከትለው ለህዝብና ለሀገር ጥቅም መስራት የሚገባቸውን ስራዎች በአግባቡ ለመስራት የሚያስችላቸውን ግንዛቤ ያስጨብጣቸዋል ብለዋል፡፡ ስልጠናው በሠራተኛውም ሆነ በዩኒቨርሲቲው አመራሮች ዘንድ የስነ-ምግባርና የተቋማዊ ባህል ግንባታ ግንዛቤ ከማስጨበጡም በተጨማሪ፣ ሥራን በጥራትና በፍጥነት በመስራት ረገድ ከአስተሳሰብ ጀምሮ ተቋማዊ ለውጥ እስከማምጣት የሚደርስ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመናል ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ ትምህርት ክፍል መምህርት የሆኑት ወ/ሮ ገነት አበበ በዚሁ ጊዜ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ጽሑፍ የስልጠናው ዋና ዓላማ የሥራ ሥነ-ምግባር፣ የመልካም አስተዳደር፣ የተቋማዊ ባህል እና ሞራላዊ ምክንያታዊነት እንዲሁም የሥራ ውጤታማነት በትምህርት ተቋማት ውስጥ ማስገንዘብ መሆኑን ጠቁመው፣ ከስልጠናው በኋላም ሃላፊነትን የማወቅና በአግባቡ የመወጣት፣ የሥራ ተነሳሽነትና የዩኒቨርሲቲውን የሥራ ባህል እንደገና በመቃኘት ሰልጣኞች ጥሩ የሥራ ባህል እንዲያዳብሩ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል። የሥራ ላይ ስነ-ምግባር መርሆዎች ቅንነት፣ ታማኝነት፣ ግልፅነት፣ ተጠያቂነት፣ ሀቀኝነት፣ ምስጢር መጠበቅ፣ አለማዳላት እና ህግን ማክበር መሆናቸውን የዘረዘሩት መምህርቷ፣ የተቋሙ ድክመትም ሆነ ጥንካሬ የጋራ በመሆኑ፣ ተቋማዊ ባህል ለመገንባት ሁለገብ ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል።
ስልጠናው በሁለት ምድብ የተከፈለ ሲሆን፣ በሁለተኛው ዙርም የስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት አቶ እያሱ በሬንቶ የትምህርታዊ ውይይት መነሻ ሃሳብ አቅርበው በሰራተኞቹና በአመራሮቹ ተመሳሳይ ውይይት ተካሂዷል።
                                                               የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መምህራን አስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች በሙሉ

የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በዩኒቨርሲቲው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ መጽሔት በቅርቡ ለማሳተም በዝግጅት ላይ ይገኛ፡፡ስለሆነም ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ማንኛውም ልዩ ልዩ መጣጥፎች፣ለግንዛቤ የሚሆኑ መልዕክቶችን እና ግጥሞችን ወዘተ. አዲሱ የአስተዳደር ህንፃ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 10 ወይም በቴሌግራም https://t.me/sileshics እስከ መጋቢት 30/2014 ዓ.ም ለክፍሉ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

                   የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

                 27/07/2014 ዓ.ም

Relevance and Quality Assurance Directorate Organizes Training to KUE’s Academic Leaders

The Relevance and Quality Assurance Directorate of Kotebe University of Education organized a one-day training under the theme “Education Quality and Institutional Governance Nexus” for the KUE Academic leaders to help them play significant roles in ensuring the quality of education.
Honourable Dr. Birhanemeskel Tena, the President of KUE, stressed in his opening speech that the present training is unique in its kind as the issue of education quality touches everyone and every activity in the Institution. Dr. Birhanemeskel also underlined the fact that quality in education is ensured using a range of parameters and of these having teachers with professional integrity, placing priority on students as well as developing a knowledge-led system are the major ones. The President further emphasized the role of teachers in bringing quality education and creating capable citizens in a country.
Two experts from the Education and Training Authority (ETA), namely Mr.Sisay Tekle, Quality Audit, and Enhancement Senior Expert, and Dr. Dunkana Negussa, Director of Quality Audit & Enhancement Directorate, delivered their expertise-based knowledge on the topics:‘Quality in Higher Education and Governance (Leadership)’ and quality Nexus’ respectively. The presentations were followed by discussions based on questions, opinions, and views raised by the participants.
In his closing speech, Dr. Shimelis Zewdie, Academic Affairs V/President, KUE, highlighted the importance of viewing quality in higher education from three perspectives: quality in the learning-teaching process, in research, and publications as well as in basic infrastructure, which is a precursor for the first two. Adding to that, Dr. Shimelis called upon the leaders at KUE to mobilize resources, coordinate the personnel and create a system of monitoring and evaluation so as to bring about quality in the institution.
Communication Affairs Directorate
April,01,2022