ሜጋ አሳታሚና ማከፋፈያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የመጻሕፍት ስጦታ ሰጠ፡፡

ጥር 19/2014 ዓ.ም(ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ)
ሜጋ አሳታሚና ማከፋፈያ ኃ/የተ/የግ/ማህበርን ወክለው የመጻሕፍት ስጦታውን ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ለተከበሩ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ያስረከቡት አቶ ለማ አሸናፊ፣ ኮተቤ ከትናንት እስከ ዛሬ ብዙ ዜጎችን የማፍራት ሀገራዊ ተልዕኮን ላነገበው ለዚህ አንጋፋ ተቋም ማህበሩ ያበረከተው ስጦታ ትንሽ ቢሆንም መጻሕፍቱ ለተማሪዎች ካላቸው ከፍተኛ እገዛ አንፃር ሲታዩ ግን ስጦታው የማይናቅ ያደርገዋል ብለዋል፡፡ እንደአቶ ለማ ገለፃ ለዩኒቨርሲቲው በስጦታ የተበረከቱት መጻሕፍት አዳዲስና በተለያዩ የትምህርት ዘርፍ ላይ ያተኮሩ ሲሆኑ ዋጋቸው በገንዘብ ሲተመን 38 ሺህ ብር ይሆናል፡፡
ዶ/ር ብርሃነመስቀል መጻሕፍቱን ከሜጋ አሳታሚና ማከፋፈያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ተወካይ ከአቶ ለማ ሲረከቡ እንደተናገሩት ሜጋ ለተቋሙ የሠጠው መጻሕፍት ለትውልድ እንደተሠጠ የሚቆጠርና ሀገርን የማሻገር ተልዕኮ ያለው ነው፡፡
የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ቤተ-መጻሕፍትና አካዳሚክ ዶክመንቴሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገብረመስቀል ግርማ በዚሁ ዕለት መጻሕፍቱን መረከባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

በአሜሪካ ካሊፎርኒያ የሚኖሩት ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆኑት ኢንጅነር ደርብ ሸንቁጥ ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የመጻሕፍት ስጦታ አበረከቱ፡፡

ትውልደ ኢትዮጵያ የሆኑት እጩ ዶክተር ኢንጅነር ደርብ ሸንቁጥ መጻሕፍቱን ለዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት፣ መጻሐፎችን ከስድስት ሲዲዎች ጋር ለማበርከት ያነሳሳቸው ምክንያት የዜግነት ድርሻቸውን ለመወጣት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ አያይዘውም ስጦታው ለዩኒቨርሲቲው አቅም ግንባታ አስተዋፅኦ ሊያበረክት እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

መጻሕፍቱን ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና እጅ የተረከቡት የዩኒቨርሲቲው ቤተ-መጻሕፍትና አካዳሚክ ዶክመንቴሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገብረመስቀል ግርማ በበኩላቸው፣ የሀገሪቱ ዜጎች እንደዚህ አስበው ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የሚገለገሉበትን መጻሕፍት በዚህ መልኩ ማበርከታቸው ለሀገሪቱ ዕድገት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አመልክተዋል፡፡

ሌሎች በውጪው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንም የኚህን ኢትዮጵያዊ አርአያነት እንዲከተሉና የሚታወሱበትን ለሀገራቸው የሚያበረክቱ እንዲሆኑ ፕሬዚዳንቱ ጥሪ አድርገዋል።

                                                              የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በየደረጃው ካሉ የዩኒቨርስቲው አመራሮች ጋር በአዲሱ የተቋማዊ ሽግግር ፍኖተ-ካርታ ላይ ውይይት አደረገ፡፡

የቀድሞው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን በአዋጅ ቁጥር 1263/2014 ዓ.ም መወሰኑን ተከትሎ የሽግግር ሂደቱን የሚያሳይ ፍኖተ-ካርታ እንዲያዘጋጅ በዩኒቨርሲቲው የተሰየመው ግብረ-ኃይል ባዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ ላይ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል በቀን 12/04/2014 ዓ.ም. ውይይት አካሂዷል።
ሰነዱ ለዩኒቨርስቲ ካውንስሉ ከቀረበ በኃላ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል የትምህርት ዩኒቨርሲቲውን ተልዕኮ፣ አወቃቀርና አደረጃጀት በተመለከተም ለዩኒቨርሲቲው በአዋጅ የተሰጠውን ተልዕኮ ማዕከል ባደረገ አግባብ የውይይቱ ተሳታፊዎች ያቀረቧቸውን ሃሳቦችና አስተያየቶች ግብረ-ኃይሉ ግንዛቤ ውስጥ እንዲያስገባና ሰነዱ የበለጠ ዳብሮ መቅረብ እንዲችል አቅጣጫ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ሰነዱን ወደ ተግባር በማሸጋገሩ ሂደት አስፈላጊ የሆኑ የዐብይ ኮሚቴ፣ ቴክኒካል ኮሚቴ እና ሌሎች ኮሚቴዎች የማደራጀት ሥራ መሠራቱን፤ በቀጣይም የትምህርት ዩኒቨርሲቲውን የማደራጀት ሥራ ውጤታማ እንዲሆን የሚረዱ የሃገሪቱ የትምህርት ልሂቃን አማካሪ የሚሆኑበት ቦርድ እንደሚቋቋምና ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተሳታፊ የሚሆኑባቸው ቀጣይ መድረኮች እንደሚመቻቹ ገልጸዋል።
ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ አደረገ።

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን የዝናብ ዕጥረት ባስከተለው ድርቅ ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ምግብ ነክና የውሃ መያዣ ቁሳቁሶች እንዲሁም ለቤት እንስሳቱ መኖ በድምሩ ወደ አንድ ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የዓይነት ድጋፍ አድርጓል፡፡
የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ በመወከል ለቦረና ዞን አስተዳደር ድጋፉን ያስረከቡት አቶ አባይ በላይሁን በርክክቡ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ይህንን ድጋፍ በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች ሲያደርግ አጋርነቱን ለማሳየት እንደሆነ ገልፀው ዩኒቨርሲቲው በቀጣይም ችግሩን በዘለቄታዊነት ለመፍታት ከአካባቢው ማህበረሰብና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር እንደሚሰራ አስገንዝበዋል፡፡
እርዳታውን የተረከቡት የቦረና ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብዱሰላም ዋሪዮ በበኩላቸው በድርቁ ለተጎዱ ወገኖች የተደረገውን ድጋፍ በማድነቅ ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት እና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በመቀጠልም ድጋፉ በአሁኑ ሰዓት የአርብቶ አደሩን እና የእንስሳቱን ህይወት ለመታደግ እያደረግን ለምንገኘው ርብርብ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸው፣ የዝናቡ ዑደት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ በመምጣቱና በአካባቢው ላይም አስከፊ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ፣ ችግሩን በዘቄታዊነት ለመፍታት በቴክኖሎጂ መታገዘ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ባለፉት ሁለት ዓመታት በሃገሪቱ በተፈጠሩ ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ምክንያት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች አጠቃላይ የ24 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፣ በቅርቡም በደብረብርሃን ከተማ ተጠልለው ለሚገኙ ተፈናቃዮች የ1.2 ሚሊዮን ብር ዕርዳታ ማድረጉ ይታወሳል።

                                           የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

 

Kotebe Metropolitan University (KMU) Capacitates Its Leaders

As of today, KMU is delivering a two-day training to capacitate its leaders’ skills in transformational leadership, change management, leading educational institutions, professional ethics, and planning. The training also focuses on raising the awareness of the leaders on higher education legal provisions. High profile professionals and public figures, to mention, Dr. Worku Negash (the Senior Advisor to Minster, MoSHE), Prof. Yalew Endawoke (the Senior Advisor to Minister, MoSHE), and Dr. Samuel Kifle, the State Minister, MoSHE) have delivered the training and shared their living experiences so far.
It is recalled that the University has restructured its institutional organisation recently through promoting a few staff to higher leadership positions and reshuffling others on the basis of their merits.

 

KMU Develops a New Website and Web-App

www.kmu.edu.et
2nd Sept 2021
Kotebe Metropolitan University has taken an advantage of the fast and up-to-date web framework- in coordination with the ICT, Communication and English Language Departments, it has developed a new Website and web-app to its internal and international clients. The website was inaugurated by Dr. Berhanemeskel Tena, President of the University and all levels of the University administration attended the commencement.
After the presentation of the website page, he underscored that the website is progressive, and accompanied by user friendly web-app. In this and other additional baseline features, he said, this website is the unique phenomenon of this year. Team leaders of the journal developers, Dr. Yosef Beco and Mr. Gizachew Atnaf jointly stated that the technology gained modern developers from the University and there will be a plan to establish the expansion of high-tech orientated works and training of high-quality user experience. Mr. Gizachew said the University is already expanding the Digital Literary, Datacenter Network Projects and E-Student Software. Mr. Samuel Alemu, instructor of the Computer Science and Technology Department, presented the website to the community.

Reported by Corporate Communications

 

የኮሜዩ-ዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የካንሰር የጨረር ህክምና ትምህርት ከባለድርሻው አካላት ጋር በመተባበር በሀገራችን ለመጀመርያ ጊዜ የሚሰጥ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የኤፌድሪ ጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ዳግማዊ ምኒልክ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ከጤና ሚንስቴር እና ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሬዲዮቴራፒ ሕክምና ቴክኒሻኖች (RTT) የሥልጠና መርሃ ግብር መጀመራቸው ለመላው ሀገራችን በማህበራዊ ሚዲያ እጅግ እንዳስደሰታቸው  ገልጸው፣ ሥርዓተ-ትምህርቱ፣ በተለያዩ አካላት አጋርነት የተዘጋጀ፣ አሁን በስራ ላይ ያሉ ዲፕሎማ ራዲዮግራፈሮችን በመጀመሪያ ዲግሪ (RTT) ለመመረቅ የሚያስችል የ2 ዓመት ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል። ለዚህም መርኃ-ግብሩን ከግብ ላደረሱ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል፡፡

ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በበኩላቸው ተቋሙ ቀደም ብሎ በሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ሲዋቀር፣ በአዲስ አስተሳሰብና ቴክኖሎጂ የተሻለ አቅምን በመፍጠር ለከተማችን ማህበረሰብ ብቁ አገልግሎትን መስጠት መሆኑን አውስተው፣ በሽታው በህዝባችን ላይ የፈጠረው ጉዳት በቁጭት እንድናስብ አድርጎናል፤ ለዚህም ዩኒቨርሲቲያችን ለመፍትሄው በትምህርት፣ ጥናትና ምርምር ለማምጣት ይህ የሬዲዮቴራፒ ሕክምና ትምህርት አይነተኛ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የዳግማዊ ምኒሊክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን አቶ ኩማ ጌታሁን ይህ የትምህርት ዘርፍ በሃገር አቀፍም ሆነ በተቋማችን ደረጃ እየተሰጠ ያለው ለመጀመሪያ ጊዜ በመሆኑና ከሁሉም ቀዳሚ በመሆናችን ሊያስመሰግነን እንደሚገባም ገልጸው፣ በጥናትና ምርምር በማስደገፍ፣ በሃገር አቀፍ ደረጃ እየጨመረ  ያለውን የካንሰር በሽታ በከፍተኛ ደረጃ በመቆጣጠር ለመፍትሄውም ሁሉም ባለድርሻ አካላት መተባበር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡                          

በክሊንተን አክሰስ ኢንሼቲቭ የካንሰር ፕሮግራም ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ያሬድ ጥላሁን መርሃ ግብሩን በማስመልከት እንዳሉት፤ ድርጅታቸው የጨረር ህክምና ላይ ከፍተኛ ልምድ ስላለውና ራሳቸውም በሥራው ላይ በመሆናቸው ሥርዓተ ትምህሩቱ በምን መልኩ ቢሻሻል የበለጠ ውጤት እንደሚያስገኝ ከልምዳቸው አንፃር አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የ Radiotherapy Technology ትምህርት ክፍል ኃላፊ ወ/ሮ መታደል ኃይሉ እንዳሉት፤ ይህ ትምህርት በሃገራችን አዲስ እንደመሆኑ መጠን በ2013 ዓ.ም አዲስ ተማሪዎችን ተቀብለን ማስተማር ስንጀምር በይዘቶቹ ላይ የተወሰኑ ክፍተቶች ስለተመለከትንና የምናስተምራቸውም ተማሪዎች ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ሲባል ሥርዓተ ትምህርቱን ለመከለስ ተገደናል ብለዋል፡፡

በማጠቃለያም፣ ክብርት ወ/ሮ ሰሐረላ አብቡላሂ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ፣ በቀጣይነትም በዘርፉ አግባብነት ያላቸው የሙያው ባለቤቶች በሃገር አቀፍ ደረጃ በቂ ዝግጅት በማድረግ የሙያ ዘርፉ በሚፈልገውን ባለሙያዎች በማፍራት ችግሩን መቅረፍ እንደሚቻል ይታመናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

   

ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ አካሄደ፡፡

ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በሚሊኒየም ፓርክ ከተቋሙና ከአካባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር በ03/12/13 ዓ.ም አካሄደ፡፡
የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፤ የዚህን ዓመት ኢትዮጵያን እናልብስ አሻራችንንም እናስቀምጥ በሚል መርህ የዚህን ዓመት የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ተቋማችን በተለያዩ ሁለት ፕሮግራሞች ሲያከናውን መቆየቱንና አሁንም ከሴኔት አባላት፣ ከመምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች፣ እንዲሁም ከመጀመሪያ ዓመት መደበኛ ተማሪዎችና ከአካባቢው የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር በመቀናጀት የተደረገ በመሆኑ ደስታ ይሰማኛል በማለት ንግግራቸውን ጀምረዋል፡፡ በመቀጠልም ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ለነገ በእያንዳንዳችን ሕይወት ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያስከትል በመሆኑ መፅደቁን በዚያው ልክ እየተከታተልን የሃገራችንን ልምላሜ ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
እንደ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ገለፃ፤ የሃገራችንን ሥነ ምህዳሯንና ዙሪያዋን በጋራ ለመጠበቅ ሲባል በኃላፊነት እንደተከልነው ሁሉ በኃላፊነት መንከባከቡንም እንዲሁ ማድረግ ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡ ተተኪ ትውልድ የሆናችሁ የመደበኛው የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ከአካባቢው የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር አደራ ለመቀበልና የኔ የምትሉትን አሻራም ለማስቀመጥ እዚህ በመገኘታችሁ ኩራት ሊሰማችሁ ይገባል ብለዋል፡፡
የኮተቤና አካባቢው የማኅበረሰብ ክፍሎች ተወካይ አቶ ወንድሙ ግዛው መርሃ ግብሩን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፤ የኮተቤና አካባቢው ማኅበረሰብ ዋነኛ የጋራ ሃብታችን የሆነው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ብቻ ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም ሲገልፁ፤ ዛሬ ላይ ሁላችንም አንድ ችግኝ ስንተክል ጥላቻን፣ ዘረኝነትን፣ ምቀኝነትና ተንኮለኝነትን ከውስጣችን ነቅለን መጣል አለብን ሲሉ ተናግረዋል፡፡
መርሃ ግብሩ የቅድመ ምረቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት በዶ/ር መስፍን አበበ ቢሮ መሪነት መከናወኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

KMU holds kick of Conference to Launching of Journals

August 10,2021, Kotebe Metropolitan University. Honorable Dr. Brehanemeskel Tena, the President of the University remembered the university had a long culture of publication -cited JOLIS of its early days 1996-2006. He holds that publication is one of the basics for KMU as an institution of higher education that his administration has the full brace to assure quality, relevance and sustainability of the journals. He believes the exercise of publication augments staff academic acumen besides its significance to the world of science . Dr. Brehanemeskel has decleared that the publication of JOLIS will resume from four to the next issues .
Research and Community Service V/P/ Dr. Tena Bekele , to his part refers that the university is in high time to start its own journal especially now after MOSHE’s identification as Applied University .He puts that highly experienced professionals invested their time and energy bringing models and references for the realization of the documents to embark the journal.
Corporate Communications Report