KUE Hosts A Joint Workshop on Designing State-of-the-Art Teachers and Leaders Development Programmes

A two-day workshop which was jointly organised by Kotebe University of Education (KUE) and Education Development Trust (EDT) was launched today, on the 4th of August 2022 at Yod Abyssinia International Hotel. The workshop’s focus was to train KUE’s professionals on designing state-of-the-art teachers’ and educational leaders’ development programmes.
Three high-profile professionals, Dr Clare Buntic, Marion Smallbones, and Maggie Farrar from the UK, have delivered very interactive training through face-to-face and online blended approaches. At the event, Dr. Berhanemeskel Tena, the President of KUE, remarked that the workshop would eminently contribute to the achievement of the institutional mission. The President was also grateful for the contributions made to KUE by EDT in general and the professionals who delivered the training in particular.
It was learnt that KUE and EDT had signed an MoU to mainly work on developing co-funding proposals, establishing KUE’s Research and Innovation Centre, collaborating on research programmes, providing school-based training, improving the quality of education, and providing technical support in the development of career progression frameworks. It was said that the agreement would also focus on developing innovative and practice-based curricula, building the capacity of leaders through mentoring, coaching, and supporting KUE in implementing the strategic plan to achieve its mission.
                                              Communications Affairs Directorate

አዲሱ የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ አባላት ዩኒቨርሲቲውን ጎበኙ፡፡

አዲሱ የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ አባላት በ30/10/2014 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲው የስራ አመራሮች ጋር ትውውቅ ካደረጉ በኋላ በዋናው ግቢ ውስጥ እየተገነቡ ያሉ አዳዲስ ግንባታዎችን፣ ቤተ መጻሕፍትና ሌሎች የልማት እንቅስቃሴዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ስራ የአመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አባዱላ ገመዳ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አዲሱ ቦርድ አባላት ከፍተኛ የሥራ ልምድ ያላቸው በመሆኑ በለውጥ ሂደት ላይ የሚገኘውን የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ወደ ላቀ የዕደገት እና የታሪክ ምዕራፍ የማሸጋገር ታሪካዊ አደራ የተጣለባቸው መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና በበኩላቸው አዲሱ የስራ የአመራር ቦርድ አባላት ፕሮፋይል ከፍተኛ ከመሆኑም በተጨማሪ ተፅዕኖ የመፍጠር አቅም ያላቸው በመሆኑ ለዩኒቨርሲቲው ዕድገት እንደ ምቹ ሁኔታ የሚታይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሠረተ ልማት ግንባታ ረገድም ሆነ በዩኒቨርሲተው ሁለንተናዊ ዕድገት ዙሪያ የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራሮች በአዲስ መልክ ከተዋቀረው የቦርድ አባላት ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
የቦርዱ አባላት የዩኒቨርሲቲው የሽግግር ሂደት፣ የመዋቅር ሰነድ እንዲሁም የ2014 ዓ.ም የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ገለፃ ከተደረገላቸው በኋላ ውይይት አካሂደዋል፡፡
ክቡር አቶ አባዱላ ገመዳ የአዲሱ የዩኒቨርሲቲው የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ፣ የተከበሩ አቶ መለስ አለሙ ምክትል ሰብሳቢ፣ የተከበሩ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ጸሐፊ፣ ፕሮፌሰር ያለው እንዳወቅ አባል፣ ፕሮፌሰር ተስፋዬ ሰመላ አባል፣ አምባሣደር ብርቱካን አያኖ አባል፣ ዶ/ር ተመቸኝ እንግዳ አባል እና ዶ/ር ወንድወሰን ታምራት አባል መሆናቸው ታውቋል፡፡
                                                          የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
 
 
 
 
 
May be an image of 4 people, people standing and outdoors
May be an image of 10 people, people standing, tree and outdoors
May be an image of 9 people, people standing, suit and indoor

Kotebe University of Education Signs MoU with Chinju National University of Education

Kobe University of Education (KUE) and Chinju National University of Education (CUE) from the Republic of Korea signed a memorandum of understanding to jointly promote academic cooperation and strengthen educational, cultural, and technological ties that will result in a better understanding between the institutions, facilitate staff and students exchange, and hence it augments academic career, research, and community service in both universities.
During the MoU signing ceremony, Dr Berhanemeskel Tena, the President of KUE, recalled Ethiopia’s sending of more than 6,000 soldiers during the Korean War (1950-53) and said that the relationship between the two countries had shown remarkable development since then. Dr. Berhanemeskel Tena also indicated that the MoU that KUE and CUE signed is another milestone for the long-standing relationship between the Ethiopian and Korean People and the government of the two nations which has already established strong relations and cooperation with the blood and bones of our forefathers.
The cooperation promotes teaching-learning endeavours, and research projects to be conducted said Dr Berhanemeskel.
On her part, Professor, Kim Hyun Joo, the Head professor of the delegation, said that the collaboration with KUE expands CUE’s scope in the international cooperation network.
Besides, the Professor expressed that the current project aimed at developing teacher education, reinforcing and improving basic education in both Ethiopia and Korea, and it would be funded by Korea International Cooperation Agency (KOICA).
                         Communications Affairs Directorate
May be an image of 3 people, people standing and text that says "전주교육대학교 S OPIA"May be an image of 3 people and people standing
May be an image of 11 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of 3 people, people standing and text that says "REVERSITYO EDUCATION CONS MIC A JO ON ACA KOTP THE FEDE 진주교육대학교 ATIVE MEETING RATIO BETWEEN EDCT FATION, ROE OF ETHIOPIA CHINJU UCATION,"May be an image of 15 people and people standingMay be an image of 15 people, people standing and indoorMay be an image of 3 people, people standing and text that says "전주교육대학교 S OPIA"May be an image of 3 people and people standingMay be an image of 2 people and people standing
May be an image of 11 people, people standing and indoor

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካል ጉዳተኛ ለሆነችው ተማሪ ሠላማዊት ጎርፉ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ፡፡

ሰኔ 06/2014 ዓ.ም
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካል ጉዳተኛ ለሆነችው ተማሪ ሠላማዊት ጎርፉ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን ሰኔ 06/2014 ዓ.ም ድጋፍ አድርጓል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የተከበሩ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና ስጦታውን በሰጡበት ወቅት እንዳሉት፤ ተማሪዋ ስትጠቀምበት የነበረው ዊልቸር በጣም ከማርጀቱ የተነሳ ለበርካታ ጉዳቶች ዳርገዋት እንደነበር ገልፀው፤ የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ካውንስል በወሰነው መሠረት ተማሪዋ ካለባት ተደራራቢ የሆኑ ችግሮች አንፃር የዊልቸር እንዲሁም የሳምሰንግ ታብሌት ስልክ ተገዝቶ በድጋፍ የተበረከተላት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ተማሪ ሠላማዊት ጎርፉ እግሮቿንና እጆቿን እንደፈለገች ያለማንቀሳቀስ ችግር፤ እንዲሁም የመናገር ችግር ያለባት ብትሆንም ይህንን ሁሉ ተደራራቢ ጉዳቶች ችላ ትምህርቷን በጥሩ ሁኔታ እየተከታተለች በመሆኑ ስጦታው ይገባታል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል፡፡
ስጦታው የተበረከተላት ተማሪ ሠላማዊት ጎርፉ በጂኦግራፊ ትምህርት ክፍል የመደበኛው መርሐ ግብር የመጀመሪያ ዲግሪ የ3ተኛ ዓመት ተማሪ መሆንዋን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 8 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of 7 people, people sitting, people standing and indoorMay be an image of 9 people, people sitting, people standing, footwear and indoor

ኮትዩ ለአብርኆት ቤተ መጻሕፍት መጽሐፍትን በስጦታ አበረከተ።

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተቋቋመው ለአብርኆት ቤተ መጻሕፍት፣ መጽሐፍትን እንዲያሰባስብ ኃላፊነት በተሰጠው በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በኩል ግንቦት 2 ቀን 2014 ዓ.ም ከጉድለቱ ሦስት መቶ ሃምሳ አምስት መጻሕፍትን በስጦታ አበርክቷል።
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ስጦታውን በማስመልከት እንደተናገሩት፣ ተቋማችን ከሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የተውጣጡ በግምት ዋጋቸው ሰባት መቶ ሰባ ሺህ ብር የሚሆን ሦስት መቶ ሃምሳ አምስት መጻሕፍትን ለአብርኆት ቤተ መጻሕፍት በስጦታ ማበርከቱን ገልጸው፣ መጽሐፍት በትውልድ ቅብብሎሽ ለዘመናት ስለሚቆዩ ስጦታው ለትውልድ የተበረከተ እንደሆነ አድርጎ መውሰድ ይቻላል ብለዋል። ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም አንባቢ ትውልድ ለመገንባት በሀገር ደረጃ በቂ ቤተ መጻሕፍት ሊኖሩ እንደሚገባ የገለጹ ሲሆን የተሠጡት መጽሐፍት ከአንደኛው ቤተመጽሐፍታችን ወደሁለተኛው ቤተመጽሐፍት እንደተሠጡ የሚቆጠር ነው ብለዋል። አያይዘው እንደገለፁት የሕዝባችንን አብሮነት እውን ለማድረግም የተማረ ትውልድ የመገንባትን አስፈላጊነት እንዲሁም ሃሳብን በጉልበት ከመሞገት ይልቅ በንባብ በታገዘ ዕውቀት መሞገት፣ ከስሜታዊነት ይልቅ የሰከነ ሕይወት ለመኖር እንደሚያስችል አብራርተዋል። የአብርኆት ቤተ መጻሕፍት እንደ ስሙ ሁሉ ትልቅ ሆኖ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲታወቅ ሁላችንም የድርሻችንን መወጣት እንደሚገባንና ለኅብረተሰባችንም እንዲህ ዓይነት ቤተ መጻሕፍቶችን በብዛት መገንባት እንደሚገባን ፕሬዝዳንቱ አሳስበዋል።
የዩኒቨርሲቲው የቤተ መጻሕፍትና አካዳሚክ ዶክመንቴሽን ዳይሬክተር አቶ ገብረመስቀል ግርማ የመጻሕፍት ስጦታውን በማስመልከት እንዳሉት፣ አብርኆት ቤተ መጻሕፍት ሁሉንም የማኅበረሰብ ክፍል ለማገልገል ተብሎ የተቋቋመ በመሆኑ የተቋማችን የቤተ መጻሕፍት ተጠቃሚዎች በስፋት የሚገለገሉባቸውን መጻሕፍት ለዚህ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት አካፍለናል ብለዋል። የተደረገው ስጦታም በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ካለን ላይ የማካፈል እና በጋራ የመቆምን አስፈላጊነት ያሳየ ከመሆኑም ባሻገር፣ የማኅበረሰቡን የአስተሳሰብ ደረጃ በመገንባት በኩል ሰፊ አስተዋፅኦ እንዳለውም አያይዘው ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የውጪ ቋንቋዎች ማኔጂንግ ኤዲተርና በተቋሙ ውስጥ በአሁኑ ሰዓት የአብርኆት ቤተ መጻሕፍት የመጽሐፍት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ በመሆን እየተጉ የሚገኙት አቶ ግዛቸው ደርብ ዩኒቨርሲቲው ለአብርሆት ቤተመጻሕፍት ላደረገው የመጻሕፍት አበርክቶ ከልብ አመስግነው፣ ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትም የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ፈለግ እንዲከተሉ ጠይቀዋል።
                                     የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of book

የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ የጀመረው ዕውቀትን የማጋራት መርሐ ግብር ለአካዳሚክ እውቀት ዕድገት ጠቃሚ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ።

ሚያዝያ 25/2014 ዓ.ም
የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ዕውቀትን የማጋራት መርሐ ግብሩን በ25/08/2014 ዓ.ም ባካሄደበት ወቅት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ጊ/ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሽመልስ ዘውዴ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር፣ ፋካልቲው የጀመረው እውቀትን የማጋራት መርሐ ግብር ለአካዳሚክ እውቀት ዕድገት ጠቃሚ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል። የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ እንቅስቃሴውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሰፋ እና የተለያዩ ተቋማትን እያሳተፈ መምጣቱን የጠቀሱት ዶክተር ሽመልስ፣ ለአካዳሚክ ዕውቀት እድገት በየጊዜው የሚደረግ አካዳሚያዊ የሆነ የውይይት መነሻ ሐሳብ መኖር ወሳኝ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እና የዕለቱ ዕውቀትን የማጋራት መርሐ ግብርም ስኬታማ እንዲሆን ያላቸውን መልካም ምኞት ገልፀዋል።
የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ዲን ዶ/ር ኃይለሚካኤል ሙሌ በበኩላቸው፣ ፋካልቲው በዕቅዱ መሠረት የምርምር ጉባኤ፣ የእውቀት ማጋራት መርሐ ግብሮችን፣ የቢዝነስ ዜና መጽሔት እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ተግባራትን በመምህራን እና በተማሪዎች አማካኝነት እያከናወነ ነው ብለዋል። የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ፈር ቀዳጅ በመሆን የጀመራቸውን ልዩ ልዩ ተግባራትንም አጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ዲኑ፣ የምርምር ሥራ ውጤት ለአካዳሚክ ማህበረሰብ ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ የህብረተሰቡን ችግር መፍታት እና በጥቅም ላይ መዋል እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የፋካልቲው መምህር የሆኑት ዶክተር ያኪን አሊ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ የዋጋ ንረት በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ መፍትሔ የሚያሻው መሆኑን የገለፁ ሲሆን፣ መምህር ይልቃል ዋሴ ደግሞ የሀገሪቱ መዋቅራዊ ለውጥ ወደ አገልግሎት አሰጣጥ ያዘመመ በመሆኑ ከሥራ ዕድል ፈጠራ አንፃር ውስንነት ስለሚኖረው የግብርና ምርት እና ምርታማነትን በመጨመር አገልግሎትን ማስፋት እና ወደ ፋብሪካ እና ኢንዱስትሪ መቀየር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በቀረቡት ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የውይይቱ መርሐ ግብር ሲጠናቀቅ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ፋካልቲ ዲን ዶ/ር ኃይለሚካኤል ሙሌ ፋካልቲው በቀጣይ ሀገር ዓቀፍ መድረክ ለማዘጋጀት ማቀዱንም አመልክተዋል።
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

10ኛው የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤት ቀን በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ።

ሚያዚያ 28/2014 ዓ.ም
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 10ኛውን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤት ቀንን ባከበረበት ወቅት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ማቲማቲክስ ትምህርት (STEM Education) ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ፣ የበዓሉ ዋና ዓላማ 21ኛውን ክፍለ ዘመን የሚመጥን የሰው ኃይል በማፍራት የህብረተሰቡን ችግሮች በዘለቄታዊ ሁኔታ የሚቀርፉ የሳይንስ ውጤቶችን በተሻለ መንገድ ማቅረብ እንደሆነ ገልጸዋል። ዕለቱን በተማሪዎች መካከል ውድድር በመፍጠር ማክበርም ይህንን ዓላማ ከማሳኪያ መንገዶች አንዱ እና ዋነኛው መሆኑን አስገንዝበዋል።
በዚህም መሠረት በየካ ክፍለ ከተማ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችን በማሳተፍ የፈጠራ ውጤታቸውን እንዲያቀርቡ በማድረግ፣ ዕለቱን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ማክበር እንደተቻለም አመልክተዋል። በዕለቱም በክፍለ ከተማው ከሚገኙ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ከሳይንስ ሼርድ ካምፓስ 39 ፕሮጀክቶች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራ እና በአይ.ሲ.ቲ ዘርፍ ቀርበው የተወዳደሩ ሲሆን፣ ለአሸናፊዎችም ሽልማት ተሰጥቷል።
በተማሪዎች የቀረቡት ፕሮጀክቶች ተስፋ ሰጪ በመሆናቸው ፕሮጀክቶቹ ጥቅም ላይ የሚውሉበትን መንገድ ማመቻቸት ከዩኒቨርሲቲው እና ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት የሚጠበቅ መሆኑንም ዶክተር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ አስገንዝበዋል።
                                                          የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

KUE Cohosts Capacity Building Workshop on Integrated Water, Sanitation and Hygiene for ONE HEALTH

Kotebe University of Education, with Bahir Dar University, hosted a three-day workshop aimed at training project participants on the application of Problem-Oriented Project-Based Learning (POPBL) and curriculum design as well as the development of the joint MSc program on IWS4ONEHEALTH as part of the project funded by NORPART—Norwegian Partnership Programme for Global Academic Cooperation on May 3, 2022, at Best Western Plus Hotel, Addis Ababa.
Dr Birhanemeskel Tena, the President of KUE, in his opening speech, thanked NORPART for funding the project which allows collaboration and partnership between the North partners (University of South-Eastern Norway, USN) and Norwegian University of Life Sciences, NMBU) and the South partners (Kotebe University of Education, Jimma, and Bahir Dar Universities) in staff exchange and student mobility. Dr Birhanemeskel also emphasized that KUE is the only education university in Ethiopia, and it contributes to the promotion of quality education as well as the internationalization of the study program which are components of the NORPART project. In addition, the President pointed out that he envisaged the collaboration between the North and South partner universities will be further developed and consolidated.
In the workshop, Dr Eshetu Janka, project coordinator at the University of South-Eastern Norway (USN), introduced the project and the new MSc program to the attendants, while Professor Sheri Bastien, a project participant from the Norwegian University of Life Sciences (NMBU), presented a lecture on the concept of WASH4ONEHEALTH. The presentations were followed by discussions based on questions and insights raised from the members of the project and participants from key stakeholders.
The seminar is expected to continue up to May 6 dwelling on issues pertinent to the project implementation and curriculum development for the joint MSc program and will be accompanied by a field visit to selected sites, such as Addis Ababa Waste Water Treatment Plant and Waste-to-Energy Facility. It is also understood that the project period is five years, and it ends in December 2026.
                            Communications Affairs Directorate

ማስታወቂያ

25/08/2014 ዓ.ም

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የተመዘገባችሁ ሁሉ የመግቢያ ፈተና ከሚያዝያ 29-30/2014 ዓ.ም ሲሆን የማመልከቻ ክፍያ 100 ብር ያልከፈላችሁ ከፈተናው ቀን በፊት በCBE 1000449424658 ከፍላችሁ ለፋይናንስ ክፍል ገቢ እንድታደርጉ እያሳሰብን የፈተናችሁ ፕሮግራም ከታች በተቀመጠው መሰረት መሆኑን እንገልፃለን::

ማሳሰቢያ: ተማሪዎች “Official transcript ” ከተመረቃችሁበት ዩኒቨርሲቲ ለማስላክ ዝግጅት ብታደርጉ።