የኮትዩ አስተዳደር ካውንስል የዩኒቨርሲቲውን አዲስ ሎጎ በአብላጫ ድምፅ መረጠ።

የቀድሞው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በአዋጅ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ተብሎ መሰየሙን ተከትሎ፣ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል በሁለት ባለሙያዎች የተዘጋጁ ዓርማዎች ወይም ሎጎዎች ላይ ሚያዝያ 19 ቀን 2014 ዓ.ም ውይይት ከአካሄደ በኃላ፣ የዩኒቨርሲቲውን አዲሱን ተልዕኮ እና አወቃቀር በተሻለ ደረጃ ያንጸባርቃል ያለውን ሎጎ በአብላጫ ድምፅ መርጧል።
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በስነስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ከዩኒቨርሲቲው የአዲሱ ስያሜ ለውጥ ጋር ተያይዞ አዲስ ዓርማ (ሎጎ) በማስፈለጉ፣ ልምድ ያላቸውን ሁለት የዘርፉ ባለሙያዎች ተጋብዞ የዓርማው ስራ መከናወናቸውን ገልፀው፣ ስራውም የተለያዩ የዝግጅት ሂደቶችን ካለፈ በኋላ፣ በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል አባላት ውይይት እና ትችት እንዲካሄድበት መቅረቡን ተናግረዋል።
እንደ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ገለፃ፣ በዚህና በቀጣይ ዓመታት የዩኒቨርሲቲያችን አዲሱ ስያሜና ተልዕኮው ላይ አተኩረን መሥራት እንደሚጠበቅብንና የመምህርነትን ሙያ ተማሪዎች ፈልገው የሚገቡበት ብቻ የማድረግ ኃላፊነት የሁሉም የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች መሆኑን በአጽንዖት ተናግረዋል።
በቅርቡ ህይወታቸው ያለፈው የአርትና ሚዩዚክ የት/ት ክፍል ባልደረባ በነበሩት በአቶ ታደሰ የተሰሩ አራት ሎጎዎች በልጃቸው በወ/ሮ ፌቨን ታደሰ በኩል፣ በአርክቴክቸር ምህንድስና ት/ት ክፍል መምህሩ በአቶ ፍሬው ዘሪሁን ደግሞ አምስት የተለያዩ ስራዎች የቀረቡ ሲሆን፣ በመጀመሪያው ዙር በድምፅ ብልጫ ከሁለቱ ባለሙያዎች ስራዎች አንድ አንድ ተመረጡ። በመቀጠልም፣ ከሁለቱ ሎጎዎች አንዱን ለመምረጥ በተደረገው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል አባላት በአቶ ፍሬው ዘሪሁን የተሰራውን ሎጎ በአብላጫ ድምፅ አሳልፏል።
በአብላጫ ድምፅ የተመረጠው ስራ በዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል አባላት የቀረቡትን ግብዓቶች በማካተት፣ የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ሎጎ ሆኖ በቅርቡ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል።
ከዚሁ ጋር አያይዘው ፕሬዝዳንቱ እንደገለፁት፣ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲው የሚቀበለው በፈተና በመለየት በመሆኑ፣ በትምህርት ጥራት ዳይሬክቶሬት ስር የመግቢያ ፈተና ማስተባበሪያ ቢሮ ተደራጅቶ የዝግጅት ሥራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል፤ በመቀጠልም ዩኒቨርሲቲው በአዲሱ ስያሜው አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን አጠናቆ፣ የተማሪዎችን መምጣት በመጠባበቅ ላይ መሆኑን እና የሚመለከታቸው የስራ ክፍሎችም ቀሪ ተግባራትን ማከናወን እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
 

ማስታወቂያ!

በ2014 ዓ.ም ወደ ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ሚያዝያ 28 እና 29/2014 ዓ.ም ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ወደ ዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ
  •  የ1ዐኛ እና 12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሰርተፊኬት
  • ከ9-12 ክፍል የተማራችሁበትን ትራንስክሪፕት
  •  4 ፓስፖርት ሳይዝ ፎቶግራፍ
  •  አንሶላና ብርድልብስ
  • የስፖርት ልብስና ጫማ
ይዛችሁ እንድትመጡ እያስታወቅን ከላይ ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጡ ተማሪዎችን የማናስተናግድ መሆኑን እናስታውቃለን።
ሬጅስትራርና አልሙናይ ማናጅመንት ዳሬክቶሬት

ዩኒቨርሲቲው ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ ተማሪዎችን በውድድር ተቀብሎ ማስተማር ሊጀምር ነው::

ሚያዝያ 11/2014 (ዋልታ) ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተማሪዎችን በውድድር ተቀብሎ ማስተማር ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡

የቀድሞው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ከወራት በፊት በአዋጅ ወደ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መቀየሩ ይታወሳል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ብርሀነመስቀል ጠና (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ባለመኖሩ ለትምህርት ጥራት መጓደል አንድ ምክንያት ሆኖ መቆየቱን ጠቅሰው ችግሩን ለማቃለል ሲባል ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እውን መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም በተለያዩ ችግሮች እየተፈተነ የሚገኘውን የኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ ለማከም ከወራት በፊት ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ትልቅ ኃላፊነት ወስዶ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል።

የትምህርት ዩኒቨርሲቲው የመምህራንን ትምህርት ዋነኛ ምሰሶ በማድረግ የትምህርት አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ አማካሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎችን ማፍራት ላይ አተኩሮ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መንገድና መዳረሻ ምን እንደሆነ የሚያሳይ ፍኖተ ካርታ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ከነባር የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በተጨማሪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚመደቡለትን ተማሪዎች ተቀብሎ ለማስተማር መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ ግን ዩኒቨርሲቲው ዓላማውን ለማሳካት ያስችለው ዘንድ ተማሪዎችን በፈተና አወዳድሮ በመቀበል ማስተማር ይጀምራል ብለዋል።

Source: Walta TV

የ2014 ዓ.ም የ2ኛ ድግሪ ትምህርትን በተመለከተ

በ2014 ዓ.ም ዩኒቨርስቲያችን ከሜትሮፖሊታን ወደ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ መቀየሩን ተከትሎ የ2014 ዓ.ም ምዝገባ መተላለፉ ይታወቃል። በመሆኑም አዳዲስ የ2ኛ ድግሪ ፕሮግራሞች በ”Masters of Education” በቅርቡ ምዝገባ ለመጀመር ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑን እየገለጽን፣ ቀደም ብሎ ምዝገባ የተካሄደባቸው የ2ኛ ድግሪ ፕሮግራሞች ምዝገባው በ”Online” እስከ ሚያዝያ 18/2014 ዓ.ም መቀጠሉን እናሳውቃለን።
ማሳሳቢያ: ከዚህ በፊት በ”Online” ለተመዘገባችሁ ለምዝገባ የከፈላችሁት ብር ታሳቢ የምናደርግ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
– ለፕሮግራሞቹን ዝርዝርና የማመልከቻ ሊንክ/የሚቀጥለውን ማስፈንጠርያ ይጫኑ::
– ለበለጠ መረጃ: +251118723289 ወይም
– የየኮሌጅ ሬጂስትራር በአካል በመገኘት ይጠይቁ።
                                                                                               የድህረ ምረቃ ት/ቤት

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የአፈፃፀም መመሪያ ላይ ተወያየ።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች የትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አፈፃፀም መመሪያ ዙሪያ ላይ መጋቢት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ውይይት አካሄዱ።

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሽመልስ ዘውዴ ለውይይቱ የመነሻ ሃሳብ ባቀረቡበት ወቅት፣ ለመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች የተዘጋጀው የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን በዩኒቨርሲቲዎች መካከልም የተወዳዳሪነትን መንፈስ ያጎለብታል ብለዋል፡፡ ዶክተር ሽመልስ በመቀጠልም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሩቃን ገበያው የሚፈልገውን አቅምና ብቃት ያሟሉ መሆናቸውን በፈተና መፈተሽ አስፈላጊ በመሆኑ፣ ይህ የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አሰጣጥ መመሪያ መዘጋጀቱን አስረድተዋል፡፡

የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የተከበሩ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና በዚሁ ጊዜ በሰጡት አስተያየት የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አሰጣጥ መመሪያው ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራንና ተቋማትም ተወዳዳሪ እና ብቁ ሆነው የሚገኙበትን አሰራር ስለሚፈጥር፣ ለአተገባበሩ ልዩ ትኩረት መስጠትና በዩኒቨርሲቲያችን ደረጃም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል፡፡

በመመሪያው ላይ በተደረገው ውይይት ተሳታፊ የነበሩት መምህራንም የትምህርት ጥራትን ለማምጣት የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና አሰጣጥ መመሪያውን ከመተግበር ባሻገር ሥርዓተ ትምህርቱን ማሻሻል፣ የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላና የትምህርት አሰጣጥ መርሐ-ግብርን ማስተካከል፣ ለትምህርት ጥራት የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ማሟላት፣ ጊዜው አጭር እና ውሳኔውም የፈጠነ በመሆኑ፣ መመሪያውን የሚያስፈፅም ራሱን የቻለ ጽሕፈት ቤት በዩኒቨርሲቲያችን ደረጃ ማቋቋም አስፈላጊ ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

Relevance and Quality Assurance Directorate Organizes Training to KUE’s Academic Leaders

The Relevance and Quality Assurance Directorate of Kotebe University of Education organized a one-day training under the theme “Education Quality and Institutional Governance Nexus” for the KUE Academic leaders to help them play significant roles in ensuring the quality of education.
Honourable Dr. Birhanemeskel Tena, the President of KUE, stressed in his opening speech that the present training is unique in its kind as the issue of education quality touches everyone and every activity in the Institution. Dr. Birhanemeskel also underlined the fact that quality in education is ensured using a range of parameters and of these having teachers with professional integrity, placing priority on students as well as developing a knowledge-led system are the major ones. The President further emphasized the role of teachers in bringing quality education and creating capable citizens in a country.
Two experts from the Education and Training Authority (ETA), namely Mr.Sisay Tekle, Quality Audit, and Enhancement Senior Expert, and Dr. Dunkana Negussa, Director of Quality Audit & Enhancement Directorate, delivered their expertise-based knowledge on the topics:‘Quality in Higher Education and Governance (Leadership)’ and quality Nexus’ respectively. The presentations were followed by discussions based on questions, opinions, and views raised by the participants.
In his closing speech, Dr. Shimelis Zewdie, Academic Affairs V/President, KUE, highlighted the importance of viewing quality in higher education from three perspectives: quality in the learning-teaching process, in research, and publications as well as in basic infrastructure, which is a precursor for the first two. Adding to that, Dr. Shimelis called upon the leaders at KUE to mobilize resources, coordinate the personnel and create a system of monitoring and evaluation so as to bring about quality in the institution.
Communication Affairs Directorate
April,01,2022

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ፤ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከዚህ በታች በተጠቀሱት ፕሮግራሞች የግል
(
Tuition Fee-Paying Study Applicant’s) በመደበኛ ፕሮግራም (ጀነሪክ እና ፖስት ቤዚክ) እና በድህረ ምረቃ ፕሮግራም በመደበኛ
እና በእረፍት ቀናት በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ትምህርታቸውን መከታተል የሚፈልጉ አመልካቾችን ተቀብሎ ለማስተማር
ዝግጅት ያጠናቀቀ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው፡፡
አመልካቾች የሚከተሉትን የቅበላ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
1. የመሰናዶ ትምህርት ያጠናቀቁ እና ቅድመ-ምዝገባ ወቅት የትምህርት ሚንስቴር ለትምህርት ዘመኑ ያሳወቀውን የመቁረጫ
ነጥብ ማሟላታቸው፤ የተረጋገጠ እና ማሟላት የሚችሉ፤ [ለ አራት አመት ፕሮግራም (Generic Program].
2. ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም የተመረቁ የጤና ባለሙያዎች ከሰለጠኑበት የሙያ መስክ ጋር በአዲሱ
የትምህርት ፖሊሲ በደረጃ 4 ወይንም በቀድሞው 10+3 ወይንም 12+2) ያጠናቀቁ ሆነው በሙያው ደረጃ 4 የብቃት
ማረጋገጫ ምዘና (COC level 4) ተፈትነው ያለፉበትን፤ እንዲሁም በሙያው ቢያንስ የአንድ ዓመት የስራ ልምድ ያላቸው
መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች በድጋሜ-ምዝገባ እለት ማቅረብ የሚችሉ፤ [ለ ፖስት ቤዚክ ፕሮግራም (Post Basic
Program) ].
3. ከውጭ ሃገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃ ያላቸው አመልካቾች ከሆኑ፤ ከኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የአቻ
ግምት አሰርተው፤ ለመጀመሪያ ዲግሪ ማመልከት ያሚያስችል ማስረጃ በድጋሜ-ምዝገባ እለት ማቅረብ የሚችሉ፤

4. ለድጋሜ-ምዝገባ የተመዘገቡ አመልካቾች በኮሌጁ የሚዘጋጁትን የመግቢያ ፈተናዎች መውሰድ እና ማለፍ የሚጠበቅባቸው
ይሆናል፡፡
ማሳሰቢያ
በቅድመ-ምዝጋባ ወቅት ምንም አይነት የማመልከቻ ክፍያ የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡
ዳግም-ምዝገባ የሚከናወነው፤ የ2014ዓ.ም የ 12ኛ ክፍል ትምህርት ሚንስቴር ለትምህርት ዘመኑ ያሳወቀውን የማለፊያ
ነጥብ ከተገለጸ በኋላ በኮሌጁ በአካል በመገኘት ይሆናል፡፡
እጩ አመልካቾች በኮሌጁ የሚሰጡ መደበኛ ፕሮግራም የጀነሪክ እና ፖስት ቤዚክ መደበኛ ፕሮግራሞችን ፤ ከታች
ከተያያዘው የጎግል ፎርም ሊንክ ገብተው ማየት ይችላሉ፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ እጩ አመልካቾች፤ከታች የተጠቀመጠውን የማመልከቻውን ማስፈንጠሪያ(
link) ተጠቅመው ቅድመ ምዝገባ ማከናወን የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ለበለጠ መረጃ ከዩኒቨርሲቲው ድህረ-ገጽ http://www.kmu.edu.et, Facebook ገጽ:
https://www.facebook.com/ww.kmu.edu.et ፣ በኮሌጁ ኢሜል አድራሻ: meneilk.hsc@kmu.edu.et ፣ከኮሌጁ
ተማሪዎች ቴሌግራም ገጽ፡ KUE Menellik Medical & Health Science College Student’s channel (link:
https://t.me/kmumhsc በተጨማሪም ከ”ዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሠራተኞች” ቴሌግራም ገጽ
ማግኘት ይችላሉ፡፡
[Access the Online Application Form] https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfwoA2iMYqKoSSPWzK6vR5K45GGEELZaL9fL5m6TMB4xV9-4Q/viewform
[Access the online Downloadable Application Form] https://docs.google.com/document/d/1GSJ2_24BiLq8SMYVsrTGKUVtX5zps-jRiFCA0JX5Rk8/edit?usp=sharing
የቅድመ-ምዝገባ ማመልከቻ ጊዜ ከመጋቢት 01-07-2014ዓ.ም እስከ መጋቢት 10-07-2014 ዓ.ም 12፡00 ሰዓት ብቻ
ማመልከቻ የምንቀበል ይሆናል፡፡
ለግንዛቤ
በጤና ሚኒስቴር የጤና ባለሙያዎቸ ብቃት ምዘናና ፈቃድ ዳይሬክቶሬት በሚሰጠው የብቃት ምዘና ፤የኮሌጁ ተማሪዎች
በአማካኝ መጠነ-ማለፍ
(Pass Rate) ከ 95% በላይ ፤ ያስመዘገበ መሆኑ፤ ተቋሙን ተመራጭ ያደርገዋል፡፡
ኮሌጁ ማሀበረሰቡን ማገልገል አላማው በመሆኑ፤ ከተማሪዎችና ወላጆች የሚጠይቀው ከመማር ማስተማር ወጪ ውስጥ የትምህርት
ወጪ ብቻ መሆኑ፤
ዋና ዋና የትምህርት ክፍያዎች በቀጣይ በተቀመጠው ሰንጠረዥ መሰረት ይሆናሉ፡፡


ተ.ቁ የክፍያ አይነት የክፍያ ተመን
1. የማመልከቻ ክፍያ (በመልሶ ምዝገባ) 100
2. የትምህርት ክፍያ በክሬዲት ለቲዎሪ አወር 95
3. ለሰርቶ ማሳያ፣ ተግባር ልምምድ በክሬዲት አወር 63.33

በኮሌጁ የሚሰጡ ፕሮግራሞች ዝርዝር

S.NO LIST OF DEPARTMENT MODALITY DURATION OF STUDY /YEAR
1 Nursing Generic 4
Post basic 2/1/2
2 Medical Laboratory Science Generic 4
Post basic 2/1/2
3 Medical Radiology Technology Generic 4
Post basic 2/1/2
4 Pharmacy Generic 5
Post Basic 3
5 Psychiatry Nursing Generic 4
Post Basic 2/1/2
6 Midwifery Generic 4
Post Basic 2/1/2

 

7 Human Nutrition Generic 4
8 Health Informatics Post Basic 2/1/2
9 Family Health Post basic 2/1/2
10 Emergency and Critical Care Nursing Post basic 2/1/2
11 Surgical Nursing Post basic 2/1/2
12 Pediatrics and Child Health Nursing Post basic 2/1/2
13 Neonatal Nursing Post basic 2/1/2
14 Operative Theater Nursing Post basic 2/1/2
15 Anesthesia

Post basic

Generic

3

4

 

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ፤ የዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከዚህ በታች በተጠቀሱት ፕሮግራሞች የግል (Tuition
Fee-Paying Study Applicant’s
) በመደበኛ ፕሮግራም (Regular እና እረፍት ቀናት (Weekend) በ2014ዓ.ም የትምህርት ዘመን
ትምህርታቸውን መከታተል የሚፈልጉ አመልካቾችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት ያጠናቀቀ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው፡፡
አመልካቾች የሚከተሉትን የቅበላ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
1. እውቅና ካለው ተቋም በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁና ከሚያመለክቱበት የትምህርት መስክ ጋር ዝምድና ያለው የት/ት ዝግጅት
ያላቸው፤
2. ከውጭ ሃገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃ ከሆነ፤ ከኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የአቻ ግምት አሰርተው፤ ለሁለተኛ
ዲግሪ ማመልከት የሚያስችል ማስረጃ በድጋሜ-ምዝገባ እለት ማቅረብ የሚችሉ፤
3. ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ከድጋሜ ምዝገባ በኋላ ማቅረብ የሚችሉ፤
ማሳሰቢያ
በቅድመ-ምዝገባ ወቅት ምንም አይነት የማመልከቻ ክፍያ የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ዳግም-ምዝገባ እና የመግቢያ ፈተና ጊዜ በማስታወቂያ ሰሌዳ ወይንም በሌሎች የተግባቦት ዘዴዎች የሚገለጽ ሆኖ አመልካቹ/ቿ
በኮሌጁ በአካል መገኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡
ለድጋሜ-ምዝገባ የተመዘገቡ አመልካቾች በኮሌጁ የሚዘጋጁትን የመግቢያ ፈተናዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡
እጩ አመልካቾች በኮሌጁ የሚሰጡ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም የመደበኛ (Regular) እና እረፍት ቀናት(Weekend)
ፕሮግራሞችን፤ ከታች ከተያያዘው Online Link ገብተው መመልከት ይችላሉ፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ እጩ አመልካቾች፤ከታች የተጠቀመጠውን የማመልከቻውን ማስፈንጠሪያ( link)
ተጠቅመው ቅድመ-ምዝገባ ማከናወን የሚችሉ እና ተጨማሪ የመመዝግቢያ ፎርም ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
2
ለበለጠ መረጃ ከዩኒቨርሲቲው ድህረ-ገጽ http://www.kmu.edu.et, Facebook ገጽ: https://www.facebook.com/ww.kmu.edu.et
፣ በኮሌጁ ኢሜል አድራሻ: meneilk.hsc@kmu.edu.et ፣ከኮሌጁ ተማሪዎች ቴሌግራም ገጽ፡ KUE Menellik Medical & Health
Science College Student’s channel (link:
https://t.me/kmumhsc በተጨማሪም ከ”ዳግማዊ ምኒልክ ህክምናና ጤና ሳይንስ
ኮሌጅ ሠራተኞች” ቴሌግራም ገጽ ማግኘት ይችላሉ፡፡
[Access the Online Application Form] https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSczyp-S1h0SFdCcS_qugwS64g3isnhQ3CwKpqiaaZacB65wtA/viewform
[Access the online Downloadable Application Form] https://docs.google.com/document/d/1k1n2SB_QynGG5fLVp3becrBxsCD4ZvuUnDfFRNH1p0o/edit?usp=sharing
የቅድመ-ምዝገባ ማመልከቻ ጊዜ ከመጋቢት 01-07-2014ዓ.ም እስከ መጋቢት 10-07-2014 ዓ.ም 12፡00 ሰዓት ብቻ ማመልከቻ
የምንቀበል ይሆናል፡፡
የትምህርት ክፍያዎች በቀጣይ በተቀመጠው ሰንጠረዥ መሰረት ይሆናሉ፡፡

ተ.ቁ የክፍያ አይነት የክፍያ ተመን /በብር
1. የማመልከቻ ክፍያ (በመልሶ ምዝገባ) 100
2. የትምህርት ክፍያ በክሬዲት አወር 900
3. የምርምር ክፍያ 10,000

በኮሌጁ የሚሰጡ ፕሮግራሞች ዝርዝር

S.No List of Department Modality Duration Of Study /Year
1 Public Health Nutrition Regular
Weekend
2
3


2 Health Service Management Regular
Weekend     
2
3
                                                                                                                  

ታላቁ የህዳሴ ግድባችን የድህነት ማሸነፊያ ተስፋችን መሆኑ ተገለጸ

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ፕሮጀከት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወቅታዊ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ የውይይት መርሐ-ግብር በ26/06/2014 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ አስተናግዷል።
ውይይቱ በተጀመረበት ወቅት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያሰሙት የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የተከበሩ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና፣ የህዳሴው ግድብ የድህነት ማሸነፊያ ተስፋችን መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በመቀጠልም ፕሬዝዳንቱ ግድቡ የይቻላል አቅም መገንቢያችን በመሆኑ ወጣቱ ትውልድ የህዳሴው ግድብ አምባሳደሮች በመሆን ለዓለም ህዝብ ስለህዳሴው ግድብ መመስከር እና በየዕለቱም መናገር ብሎም በቀጣይነት ድጋፉን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከሚመገቡት ምግብ በመቀነስ ለህዳሴው ግድብ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ሲያበረክቱ መቆየታቸውን ያስታወሱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት፣ በቀጣይም ከድህነት እና ከጨለማ ውስጥ የመውጣት አስተሳሰብ በማጎልበት በእውቀታችን፣ በገንዘባችንና በጉልበታችን አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር ተወካይ የሆኑት ዶክተር ታምራት ይገዙ በበኩላቸው ትምህርት ከድህነት ለመውጣት ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ መንግሥት ለትምህርት ልዩ ትኩረት በመስጠት እየሰራ የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በእውቀት የታነፀ እና ሀገርን ከድህነት ለማውጣት ቁርጠኛ የሆነ ትውልድ ለማፍራት በተለይ የወጣቱ ትውልድ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ወጣቱ ትውልድ ባለፉት ዓመታት ለህዳሴው ግድብ መሳካት ቦንድ በመግዛት ያሳየው የነቃ ተሳትፎ ለሀገሩ እድገት የሚቆረቆር ዜጋ እያፈራን ስለመሆኑ ምስክር ነው በማለትም ተናግረዋል፡፡
በዕለቱም ለውይይት መነሻ የሚሆኑ ሦስት ጽሑፎች ቀርበው በተማሪዎቹ ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን፣ ተማሪዎች በህዳሴው ግድብ ዙሪያ እውቀት፣ አስተሳሰብና አመለካከትን በአግባቡ በመቅረፅ እና በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች በማስረዳትና በማስተዋወቅ፣ አፍራሽ አመለካከቶችን በመመከት እንዲሁም ትክክለኛውን መረጃ በመስጠት የአምባሳደርነት ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ተብሏል፡፡ ተማሪዎችም በበኩላቸው የራሳቸውን ሚና እንደሚወጡ ገልጸዋል፡፡
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ፕሮጀከት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሄ ከዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር የተደረገው ውይይት ውጤታማ እንደነበር ጠቅሰው ተማሪዎችም ሀገሪቱን ከጨለማ ወደ ብርሃን ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት የእስካሁኑን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡
                               የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት

Kotebe University of Education Delivers Training on the Role of Teachers in Boosting STEM Education in Primary and Secondary Schools

 
Kotebe University of Education delivered a two-day training to selected primary and high school teachers in Addis Ababa on enhancing their understanding and implementation of Science, Technology, Engineering, and Mathematics (STEM) education in their respective schools, from February 21-22, 2022.
In his opening speech, Dr. Tena Bekele, V/President for Business and Development, Kotebe University of Education, remarked that STEM education is crucial for the development of a country as it encourages innovation that brings new technologies, products, and services. He also noted that the training has been prepared to inspire and support especially Science and Mathematics teachers for they shoulder greater responsibilities in realizing this endeavor.
Dr. Tewodros Mulugeta, the Director of STEM education at Kotebe University of Education, on his part, said that STEM education aids to produce creative and knowledgeable students who solve the complex and dynamic challenges that the 21st century poses. As to him, the present training focused on teachers as they are the primary stakeholders of STEM education.
The trainees spent the second day of the training visiting STEM education centers at Addis Ababa Science and Technology University.
                            Communications Affairs Directorate
                                      February 22, 2022