ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ወራሪው ጁንታ ላፈናቀላቸው ወገኖቻችን ለሁለተኛ ጊዜ ድጋፍ ሰጠ፡፡

                                                                                                                                                                    25/03/2014 ዓ.ም

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለሁለተኛ ጊዜ ለወገን አሌኝታነቱን በተግባር ለመግልፅ ያደረገው ድጋፍ በወራሪው ጁንታ ምክንያት ተፈናቅለው በደብረብርሃን ከተማ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ወገኖቻችን እንደሆነ ተውቋል፡፡ ድጋፉ ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የተሰባሰቡ ምግብ ነክ፣ አልባሳት፤ የተለያዩ ቁሳቁሶችና የግል ንፅህና መጠበቂያዎችን ያካተተ ሲሆን በገንዘብ ሲሰላ 1.2 ሚሊዮን ብር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚሁ ወቅት ወራሪ የህዝብ ጠላት በሆነው ጁንታ ታጣቂ የተፈናቀሉት ወገኖችና በጦርነቱ የተጎዱ ጄግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አባለት የተጎበኙ ሲሆን ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢያዎች ያሉትና በጦርነቱ ተጎድተው በማገገም ላይ የሚገኙ ወገኖች በተደረገው የደጀንነት ተግባር መደሰታቸውን ገልፀዋል፡፡

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕዝዳንት የተከበሩ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ለወገን አሌኝታነታቸውን ለማግለፅ በእለቱ በከተማው የተገኙ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችን በመወከል ባደረጉት ንግግራቸው የአጥፊዎች ሴራና የአውዳሚዎች ተግባር በመላው የቁርጥ ቀን ኢትዮጵያዊያን ደጀንነት መደገፍና መመከት ስላለበት ይህንኑ ተግባራቸውን ለመወጣት ዩኒቨርሲቲዎቸ እውቀትን አፍልቆ ከማስተማር ባሻገር ያላቸውን ጥሪት በማካፈል ያደረጉት አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፆ ለወደፊትም ችግሩ በዘለቄታዊነት እስከሚቀረፍ ድረስ ድጋፉ ቀጠይነት እንዳለው ተናግሯል፡፡ እንዲሁም በስፍራው ካለው የመከላከያ ሠራዊታችን ጋር በነበረው መርሀ-ግብር ላይ እንደተናገሩት ጄግኖች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ጠላትን እየመከቱ፤ ድባቅ እየመቱ፤ በአጥንታቸው ሀገርን እየገነቡ፤ ኒዮ-ኮሎኒያሊዝምን እያሸነፉ በደማቸው ደግሞ አኩሪ የድል ታሪክን እየፃፉ ስለሆኑ እጅግ ኮርተንባቸዋል ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ከአሁን ቀደም በወራሪው ጁንታ ጦርነት ምክንያት ከአፋር ክልል እና ከወሎ ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን ዩኒቨርሲቲው የአምስት ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

                                                                                                                      የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                                

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ተቋማዊ የሽግግር ሂዳትን አስመልክቶ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሄደ

                                                                                                                                                                            17/03/2014 ዓ.ም
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በዛሬው ዕለት በዋና ግቢው የተቋሙን ሽግግር ሂዳት አስመልክቶ ጥልቅ ውይይት አካሄዷል፡፡ በዚሁ ወቅት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት የተከበሩ ዶ/ር ብርሀነመስቀል ጠና የተቋሙ ታሪካዊ ዳራና ችግሮቹ እንዲሁም የወደፊት ትኩረት አቅጣጫዎቹ ላይ በማተኮር ለውይይት መነሻ የሚሆን ገላጭ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ የትምህርት ልህቀት፣ የምርምር ስርፀት፣ የዩኒቨርሲቲው መዋቅራዊ፣ መልካም አስተዳደራዊና የስራ አመራር ለውጥ፣ ማህበረሰባዊ ተሳትፎን ማሳደግ፣ ገበያ-መር በሆነ መልክ የተቋሙን ፕሮግራሞች በመቃኘትና በአዋጅ 1263/2014 የተሰጠውን የትምህርት ዩኒቨርሲቲነትን ተልዕኮ በብቃት መወጣት የተቋሙ የወደፊት የትኩራት አቅጣጫዎች እንደሆኑ ጠቁመዋል፡፡
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለሀገራችን የትምህርት ጥራት ውድቀት ምክንያቶቹና ለችግሮቹ መፍትሄ ናቸው ብለው ያሉዋቸውን ቁምነገሮች ከዘረዘሩ በኋላ የስራ መመሪያና የዩኒቨርሲቲውን የወደፊት ትኩረት አቅጣጫ ሲያመላክቱ እንደተናገሩት እያንዳንዱ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በኃላፊነትና በተቆርቋሪነት ለዩኒቨርሲቲው አዲስ በተሰጠው የትኩረት አቅጣጫ ምክክር ላይ በንቃት በመሳተፍ በአገራችን የትምህርት ጥራት ለውጥ እንዲመጣ በትጋት በመስራት ልዩ አስተዋፅኦ ማበርከት ከዩኒቨርሲቲው እንደሚጠበቅ ገልፀዋል፡፡የከፍተኛ ትምህርት ሚንስትር ዴኤታው ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው መንግስት ከዩኒቨርሲቲው የሚጠብቀው ለውጥ፣ ጥገናዊ ሳይሆን መሠረታዊ ለውጥ እንደሆነ አስምሮበት ለዚሁ ተልዕኮ ዩኒቨርሲቲው ራሱን ማዘጋጀት እንዳለበት አሳስቧል፡፡
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
 

Kotebe Metropolitan University

Kotebe University of Education (KUE) Undertakes Budgetary Training Deemed Necessary for Institutional Transformation

******************************************

As KUE prepares itself to undertake institutional transformational from Metropolitan development oriented programm to University of Education , which could be the first of its kind in the history of the Nation in a century, is giving training to its leaders on how to prepare and use the Federal programm budget. On his opening speech, Honorable Dr. Berhanemeskel Tena, the President, underling the significance of the training to the effective transition being underway, encouraged the trainees to actively participate in the training.

Experienced professionals from the Ministry of Finance are delivering the training.

                                                                                                         

                                                                                                      Communications Affairs Directorate

የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የሚሰራቸው ጥናቶችና ምርምሮች ውጤታማና ችግር ፈቺ መሆናቸው ተገለፀ፡፡

የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ መከላከል ኮሚሽን ጋር በመተባበር የአዲስ አበባ ከተማንና የአካባቢዋን የአደጋ ተጋላጭነት ለመቀነስ ባለመው የጥናት ኘሮጀክት ዙሪያ ግብዓት ለማሰባሰብ በቶኘ ቴን ሆቴል በተካሄደው አውደ ጥናት ላይ የዩኒቨርሲቲው ኘሬዝዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና፣ የቀድሞው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የአሁኑ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሚሰራቸው ጥናቶችና ምርምሮች ማህበረሰብ ተኮር፣ ውጤታማና ችግር ፈቺ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡  

ዩኒቨርሲቲው በእስካሁኑ ሂደት ከከተማው አስተዳደር ቢሮዎች ጋር በመተባበር የሰራቸው ጥናቶች በቅርቡ ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ አጠቃላይ ሂደት በማስመልከት የተሰራውን ጥናት ጨምሮ ሁሉም ጥናቶች ውጤታማ እንደነበሩ የጠቀሱት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና፣ ዩኒቨርሲቲው ጥናቶችንና ምርምሮችን ሲሰራ ለገንዘብ ብሎ ሳይሆን በተግባር የማህበረሰብን ችግር ለመፍታት አልሞ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡በተመሳሳይ መልኩ አሁን እየተሰራ ያለው ስራ የከተማዋን ችግር ሊፈታ የሚችል እንደሚሆን ያላቸውን ተስፋ የገለፁት ኘሬዝዳንቱ ይህ ጥናት የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ወደ ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከተቀየረ ወዲህ የመጀመሪያው እንደሚሆንና ለጥናቱም የእስካሁኑ ሂደት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ መከላከል ኮሚሽን ድርሻ ጉልህ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የአውደ ጥናቱን ተሳታፊዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉት የኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህብረሰብ ምክትል ኘሬዝዳንት ዶክተር ጠና በቀለ፣ ጥናቱ በሃገራችን ታሪክ የመጀመሪያውና ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት የተሰራ እንደመሆኑ ለሌሎች ከተሞችም አርአያ ስለሚሆን ለኘሮጀክቱ ስኬታማነት ግብዓት የሚሆን በእውቀት ላይ የተመሠረተ ሙያዊ አስተያየት እንዲሰጥበትም ጠይቀዋል፡፡ በዚሁ የምክክር መድረክ የጥናቱን ሂደት የሚያመለክቱ መነሻ ትልመ ጥናቶች በዶ/ር በሊና ተርፋሳ፣ በዶክተር ብርሃኑ እንደሻውና በዶክተር ቱሉ ቶላ የቀረበ ሲሆን በጥናት ቡድኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እተየሰራ ያለው ስራ ገና ከጅመሩ ብዙ የታለፈበትና በቀጣይም ሲጠናቀቅ የከተማዋን ብሎም ዙሪያዋ የሚገኙ አካባቢዎችን ችግር ለመፍታት ትልቅ ተስፋ የተጣለበት መሆኑንም የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች አስተያየት የተሰጠበት የተሳከ የውይይት መድረክ መሆኑን ለማወቅ ተችላል፡፡  

 

                                                                                                                    የኮሚዩኒኬሽንስ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት                                                            

ለአንደኛ ዓመት (አዲስ የተመዘገባችሁ) የማታና እረፍት ቀናት ዲግሪና ዲፕሎማ ተማሪዎች በሙሉ

1ኛ. ካመለከታችሁበት የትምህርት ክፍል Username እና Password ወስዳችሁ ፕሮፋይል አዘጋችታችሁ ነገር ግን ክፍያ በCBE Birr ያልከፈላችሁ ተማሪዎች ብቻ ማክሰኞ ጥቅምት 16 ቀን እና ረቡዕ ጥቅምት 17 ቀን 2014 ዓ/ም በኦንላይን ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ እና ክፍያ በCBE Birr እንድትፈጽሙ እንዲሁ

2ኛ. ትምህርት የተጀመረ በመሆኑ የኮሌጅ/ፋኩልቲ/አካዳሚ የተከታታይና ርቀት ትምህርት አስተባባሪዎች ባወጡት የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ትምህርታችሁን መከታተል እንድትጀመሩ እናሳስባለን፡፡

 

                                                                                                                                  የኮሜዩ ተከታታይና ርቀት ትምህርት ዳይሬክቶሬት

ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ፡፡

ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ (ኮሜዩ) በ2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በቅደመ-ምረቃና በድህረ-ምረቃ በቀንና በማታ መርሀ-ግብሮች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2526 ተማሪዎችን ዛሬ ጥቅምት 6 ቀን 2014 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል፡፡
የኮሜዩ ፕሬዝዳንት የተከበሩ ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በበኩላቸው የኮቭድ-19 ወረርሽኝ ጫናን እና በሀገር ሉዓላዊነት ላይ የተደቀኑ ተግዳሮቶችን ሁሉ ተቋቁማችሁ ለዛሬ ምረቃ የበቃችሁ እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን ዛሬ ሀገራችን በፈተና ውስጥ ባለችበት የተመረቃችሁ ምሩቃን ሀገራችሁን የምትከላከሉ፣ ፍትህን የምታረጋግጡ ።፣ ሌብነትን የምትዋጉ ፣ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትን የምታጎለብቱ፣ ለሀገራችሁ በየደረሳችሁበት አምባሳደሮች እንድትሆኑ ።፣ በየተመረቃችሁበትም ሙያችሁ ለሀገራችሁ ለብልጽግናዋ የድርሻችሁን የምትወጡ እንድትሆኑ ሲሉ የአደራ መልዕክታቸው አስተላልፈዋል።
ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ረገድ ያለውን ደማቅ ታሪካዊ አሻራውን እንዲያስቀጥል “ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ” ሆኖ በአዋጅ በመቋቋሙ መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ የክብር ዶ/ር አባዱላ ገመዳ ባደረጉት ንግግር የዕለቱ ምሩቃን እንደሀገርም ሆነ እንደግለሰብ ባጋጠማቸው ተግዳሮቶች ሳይገቱ በአስቸጋሪ ወቅት ሁሉንም ጫና ተቋቁመው ለመመረቅ በመብቃታቸው እንኳን ደስ አላችሁ ካሉ በኋላ በቀጣይም ምሩቃኑ ተግዳሮቶችን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም የልማትና የሰላም ጅምር ሥራዎችን በማስቀጠል ረገድ ተስፋ የተጣለባቸው መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ቀጥሎም ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ አሁን ለደረሰበት ደረጃ ላደረሱት መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በሌላ በኩል የኢፌዲሪ የውጪ ጉዳዮች ሚንስቴር ቃለ-አቀባይ የተከበሩ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለተመራቂዎቹ ባስተላለፉት መልዕክታቸው ሁሉም በሙያው ቋንቋ፣ ሀይማኖትና ዘር ሳይለው የሀገሩ አምባሳደር ስለሆነ ምሩቃኑ ልዩነትንና ብዝሀነትን እንደ ህብር ጌጥ በመውሰድ የሀገራቸው አምባሳደሮች መሆናቸውን ተገንዝበው በአንድነት ለሀገር ግንባታና ለሰላም መስፈን መስራት እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም ዩኒቨርሲቲው በትምህርታቸው ብልጫ ላመጡ ተማሪዎች ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ከመስጠት ባሻገር ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የአመራርነት እርከን ደረጃ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ዶ/ር ደመወዝ አድማሱ የዕውቅና ሽልማት ከምስጋና ጋር ሰጥቷል፡፡
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር

ለመምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች በሙሉ

             ሰኞ ጥቅምት 8 ቀን 2014 ዓ.ም ዩኒቨርሲቲያችን በአዲስ ዘመን ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን እና የዓመቱን የተማሪዎች ምርቃት በማስመልከት ኘሮግራም  ተዘጋጅቷል፡፡ ስለሆነም ከላይ በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት በዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ህንፃ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ እንድትገኙ እያሳሰብን በተለመደው መልኩ በሁሉም መስመሮች የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

                                                                                                                                                                                              ዩኒቨርሲቲው

ማስታወቂያ ለአዲስ እና ነባር ድህረ-ምረቃ ተማሪዎች

በኮተቤ ሜትሮፓሊታን ዩኒቨርሲቲ ድረገጽ ለመመዝገብ የቴክኒክ ችግር ስላጋጠመ በአጭር ጊዜ ውስጥ እስክናስተካክል እንድትታገሱን ከይቅርታ ጋር እየጠየቅን የምዝገባ ጊዜውን ለተወሰነ ጊዜ እንደምናራዝም እናሳስባለን።
ድህረ-ምረቃ እና ሬጂስትራር   ጥቅምት 04/2014 ዓም 

How to apply for a PhD and Master’s Degree (Regular, Evening or Weekend) for 2021/22 Academic Year

How to apply for a PhD and Master’s Degree (Regular, Evening or Weekend)

for 2021/22 Academic Year

Kotebe Metropolitan University would like to invite applicants for PhD and Masters’ Degree Programs to the Academic Year 2021/22(2014 E.C).

Procedures to apply:

    1. Write estudent.kmu.edu.et
    2. Click Apply Here
    3. Then Fill the Form,
    • Personal Detail(First name, Father name, Grand Father name, Gender, Martial Status, Nationality and Date of Birth
    • Apply for: Select Field of Study(program) with its modality
    • Educational background: Click Add Education and fill your Bachelor Degree’s Institution, Field of Study and CGPA
    • Select Financial Support(Government sponsored/Non-government sponsored/Self sponsored)
    • Fill Contact address( Phone and e-mail)
    • Supportive documents: Attach academic/supportive documentsmerged or converted in asingle page-Pdf format

 To attach click choose file, select and attach.

Your educational records: Degree and Transcript documents are mandatory.

    • Finally click Apply
    1. When you click Apply, you will get the following instruction to settle/pay application Fee of Birr 100.00 in CBE Birr payment system

Dear ______________

You have applied for 2021/2022 admission. Use CBE Birr payment system before the application deadline. Your Check Code is:________

How to Pay:

    1. Dial *847#
    2. Choose 5. Pay Bill
    3. Choose 5. Webirr
    4. Enter the above Checkout Code
    5. Finally Approve

Additional information

    1. Send your official transcript to Kotebe Metropolitan University Registrar P.O.Box 31248 from your previous institutions.This will also include KMU Alumni (Graduated Students).
    2. Dates of the entrance examination will be notified on the Notice Board of College/Faculty/Academy which you have applied for or you may also check the examination period from KMU website(www.kmu.edu.et)
    3. Official Transcript is mandatory to register (for Accepted students). (Otherwise, his/her acceptance to the program will be canceled)
    4. Minimum class size is required to open any program.

Notice and List of Program: look at www.kmu.edu.et

For Further info:  01118723289, PG Directorate/01118134364, RAMD