KMU Supports War Victims in two Regions of Ethiopia

18th Sept. 2021
Kotebe Metropolitan University has mobilized aids of foods, sanitary facilities, bonded mattresses and other supports to the highly vulnerable war victims of the Afar and Amhara regions. The President, Dr. Berhanemeskel Tena said that this support has been offered for the third time since the TPLF clique orchestrated war against our country and left spilling unrest across the two regions in Ethiopia. In different phases, the University’s community pledged one month salary and already provided for the GERD project; and in the same year, the staff offered additional one month salary for the Ethiopian National Defense Army. The President added that this support is life-saving assistance being transported for those affected by war. The loads to the Amhara region is led by Dr. Hailemichael Mule and to the Afar by Mesfin Wondosen. On the farewell program, the President underscored that, “Our University’s community is always committed to assist those who pay heroic sacrifice for the Unity and dignity of this great Nation!”

ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ መካከለኛ አመራሮችን በአዲስ መልኩ ማደራጀቱን አስታወቀ፡፡

መስከረም 08፣2014
ዩኒቨርሲቲው በአዲስ መልክ በሜትሮፖሊታን ደረጃ ከተዋቀረ ጀምሮ፣ በለውጥ ጎዳና እንዲጓዝ ካስቻላቸው ዋነኛው ስራዎች መካከል የአመራሮች አደረጃጀት መሆኑ ተገለጸ፡፡ በዚህም መሠረት፣ ዩኒቨርሲቲውን ባለፉት አመታት ሲመሩ የነበሩና ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት መካከለኛ አመራሮች የምስጋና ምስክር ወረቀት የተሰጣቸው ሲሆን፣ በምትካቸውም አዳዲስ አመራሮች ተመድበዋል፡፡
በርክክብ መርኃ-ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና እንደገለፁት ምደባው በውድድር እንደነበረና ምሳሌ ሊሆን በሚችል መልኩ የተከናወነ ሲሆን በርካታ ተወዳዳሪዎች ተሳትፈውበታል። ምርጫውም
ልምድን ፣ ለሥራ ያላቸውን ተነሳሽነትና ፍላጎትን መሠረት ያደረገ ነበር። ምደባው ለውጥን ማዕከል አድርጎ አዳዲስ አመራሮችን ወደፊት እንዲመጡ ያስቻለ ነው። በዚህም አዲሱ አመራር ዩኒቨርሲቲውን አሁን ከደረሰበት ደረጃ ከፍ ወዳለ ደረጃ ሊያሸጋግሩ ይችላሉ ተብለው እምነት ተጥሎባቸዋል ። በአዲስ አደራን የተቀበሉት እነዚህ አመራሮች ወደሥራ ከመግባታቸው በፊት የአመራርነት (Leadership) ሥልጠና እንደሚሠጣቸው ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል ።

Science shared campus announcement

ማስታወቂያ

ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዪኒቨርሲቲ ቀዳማዊ ምኒሊክ ሳይንስ ሸርድ ካምፓስ በ2013 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ የክልላዊ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ዉጤት ያስመዘገቡ ተማሪዊችን እንደተለመደው አወዳድሮ ለማስተማር ይፈልጋል፡፡ሙሉ ማስታወቂያውን ከዚህ በታች  ያንብቡ…

ጳጉሜ 1 “የኢትዮጵያዊነት ቀን”- በኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ ተከበረ!!

የኮተቤ ሜትሮፖታን ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በስራ ገበታቸው ላይ በመገኘት ጳጉሜ 1ን ከጠዋቱ 2:30 “ለኢትዮጵያ ክብር እቆማለሁ፤ እዘምራለሁ ” በሚል መሪ ቃል ኢትዮጵያን ከፍ በማድረግ እለቱን አክብረዋል።
በፕሬዝደንት ጽ/ቤ/ት ፊት ለፊት የተገኙት የዩኒቨርሲቲው አመራርና ሰራተኞች፣ የኒቨርሲቲዉ ተማሪዎችና የህብረቱ አመራሮችና የፌዴራል ፖሊስ ተወካዮች በጋራ በመሆን ከጠዋቱ 2:30 ላይ በመገናኘት የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙር በመዘመር እለቱን ያደመቁ ሲሆን፣ በመርኃ-ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፣ የጳጉሜ ቀናቶች ለሃገራዊ አንድነታችንና ክብር የተለየ ትርጉም እንዲኖራቸው ታሳቢ ተደርጎ የተሰየሙ መሆኑን በመግለፅ የእያንዳንዱን ቀን ስያሜ ምንነትና ትርጉም አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን በተለይም በከፍተኛ ትምህት ተቋማት ያለን ማህበረሰብ የኢትዮጵያ ክብር የተረዳ ትዉልድ ከመፍጠር አንፃር ብዙ መስራት እንዳለብን በማሳሰብ ሁላችንም ለኢትዮጵያችን ያለልዩነት በአንድነት ለመቆም ቃል የምንገባበትና በተሰማራንበት የስራ መስክ እንደመከላከያችን ለሃገራችንን ክብር ከመቸውም ጊዜ በላይ ተግተን በመስራት የተግባር ጀግንነትን እንድንጋራ አደራ የተጣለብን መሆኑን አውቀን ቃል የምንገባበት ቀን ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡