በወንድይራድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሐግብር ላይ የተገኙት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፣ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ “በመትከል ማንሰራራት!” በሚል መሪ ቃል በቅርቡ በዩኒቨርሲቲው ግቢ እና በወንድይራድ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ችግኝ መትከሉን አስታውሰው፣ በዛሬው ዕለትም የተከናወነው የችግኝ ተከላ ደግሞ “በአንድ ጀንበር 700 ሚሊዮን ችግኝ መትከል” በሚል መሪ ቃል በክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የሚያስቀጥል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በመላው ሀገሪቱ እየተካሄደ ያለውን ይህን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ መርሐግብር ተግባራዊ ለማድረግ ዛሬ የተከልናቸውን ችግኞች በመንከባከብ የተሻለች አረንጓዴ ፣ የተፈጥሮ ምህዳሯ የተስተካከለ ሀገር ለትውልድ ለማቆየት ዛሬ እንተክላለን፤ በቀጣይም የተከልነውን በቅርበት የመንከባከብ ኃላፊነት አለብን ብለዋል ፕሬዚዳንቱ።