Skip to content

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተቋማዊ የለውጥ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከመምህራን ጋር ውይይት አደረገ

(ኮትዩ ፣ ህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም) – የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ ከዩኒቨርሲቲው መምህራን እና የአስተዳደር የሥራ ክፍሎች ኃላፊዎች ጋር በዩኒቨርሲቲው የአሠራርና የለውጥ አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ የሁለት አዲስ ምክትል ፕሬዘዳንቶችን ሹመትንም አሳውቀዋል።
አዲሶቹ ምክትል ፕሬዘዳንቶች፣ የዩኒቨርሲቲውን አካዳሚክ ጉዳዮች ጽ/ቤት በምክትል ፕሬዘዳንትነት ሲመሩ በነበሩት ዶ/ር ፈቀደ ቱሊ ምትክ ዶ/ር አለባቸው ከሚሶ፤ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን የምርምርና የማህበረሰብ ጉድኝት ጽ/ቤት ሲመሩት በነበሩት ዶ/ር ኤፍሬም ተክሌ ምትክ፣ ዶ/ር ቴዎድሮስ ሙሉጌታ የተመደቡ መሆናቸው ታውቋል።
ለሁለቱ የቀድሞ ምክትል ፕሬዘዳንቶች የምስጋና እና ሽኝት፣ እንዲሁም በምትኩ ለተመደቡት አዲስ ምክትል ፕሬዘዳንቶች ደግሞ የትውውቅ መርሐግብርም ተደርጓል።
በመድረኩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ ዩኒቨርሲቲው ያለፈባቸውን ሂደቶች፣ ያከናወናቸውን ተግባራት፣ የተሰጠውን ተልዕኮ ከማሳካት አንጻር በጥናት የተለዩ ክፍተቶችን እና ክፍተቶቹን ለመሙላት የሚያስችሉ መንገዶች አቅርበው፣ ዩኒቨርሲቲው እንደ ሞዴልና ብቸኛ የትምህርት ተቋም በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ የሚጓዝባቸውን የለውጥ አቅጣጫዎች በዝርዝር አቅርበው ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *