(ኮትዩ፣ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ.ም) – ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የካ ዲስትሪክት ሲቢኢ በጄ የተባለ መተግበሪያን በመጠቀም ለዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ገንዘብ ለመበደርና ለመቆጠብ የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመወዋል።
የፊርማ ሥነስርዓቱን የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ እንግዶቹን እንኳን ደህና መጣችሁ ካሉ በኋላ፤ ባንኩ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በጋራ ለመስራት ያሳየውን ተነሳሽነት አድንቀዋል። ዶ/ር ተሾመ፣ የዩኒቨርስቲው የገንዘብ እንቅስቃሴዎች በንግድ ባንክ አካውንት በኩል ሲደረጉ መቆየታቸውን በመጥቀስ ከባንኩ ጋር የቆየ ትብብር መኖሩን አመላክተዋል።





