Skip to content

የኮተቤ የትምህርት የኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫ አካሄደ

(ኮትዩ፣ ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም)- የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት አስመራጭ ኮሚቴ ዛሬ በካሄደው ምርጫ፣ ተማሪ ኃይለአምላክ አያሌው የህብረቱ ፕሬዘዳንት፣ ተማሪ ኤልያስ ያዴታ ምክትል ፕሬዘዳንት፣ ተማሪ ሜሮን አዲሱ ጸሐፊ እንዲሁም ተማሪ መዳዊ አብዱ የሴቶች ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊ ሆነው ተመርጠዋል።
የምርጫውን ሂደት በንግግር የከፈቱት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ተሾመ ነቃጥበብ፣ የተማሪዎች ህብረት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ተማሪዎች፣ የዲሞክራሲ ስርዓትን ሂደቶች የሚለማዱበት ከመሆኑም ባሻጋር ብዙ ማህበራዊ ጉዳዮቻቸውን የሚያስፈጽሙበት አደረጃጀት እንደሆነ አስታውሰው፣ የህብረቱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት የወከሏቸውን ተማሪዎች በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡ ለዚህም የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ከጎናቸው በመሆን እንደሚደግፋቸው ጨምረው ገልጸዋል።
ምርጫውን ያስተባበሩት የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች አገልግሎት ዲን አቶ ዓባይ በላይሁን በበኩላቸው፣ የምርጫ ሂደቱን በዝርዝር ያብራሩ ሲሆን፣ የተካሄደውም ምርጫ ህዝቦች ተወካዮቻቸውን፣ ተወካዮች ደግሞ መሪያቸውን የሚመርጡበትን የእውነተኛ እና Yዲሞክራሲያዊ ምርጫ አካሄድ ማሳያ ነው ብለዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *