ጅማ ፣ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም) – በጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በፓራኦሎምፒክስ የጠረጴዛ ቴኒስ ውድድር ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን እና የሻምፒዮና ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል።
ዩኒቨርሲቲው ይህንን ድል የተቀዳጀው በመስማት የተሳናቸው የወንዶች የጠረጴዛ ቴኒስ ውድድር ሲሆን፣ በቡድን እና በጥንድ ጨዋታዎች አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲን በመርታት ነው።





