በዘንድሮው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የስፖርት ፌስቲቫል ላይ በመተሳተፍ ላይ የሚገኘው የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የእግር ኳስ ቡድን፣ ዛሬ ባደረገው ጨዋታ ተጋጣሚውን የኦዳቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ቡድንን 2-1 በሆነ ውጤት ረቷል፡፡ ቡድኑን አሸናፊ ያደረጉትን 2 ጎሎችም የቡድኑ አጥቂ አሚር ሲራጅ በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ላይ አስመዝግቧል፡፡ ትናንት ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ ጋር ባደረገው የመጀመሪያ ጨዋታው 1 አቻ የተለያየው የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ 4 ነጥቦችን […]
Read Moreበኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ትብብር በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች አፋን ኦሮሞ እና አማርኛ ቋንቋዎችን እንደሁለተኛ ቋንቋ ለሚያስተምሩ መምህራን የሥራ ላይ ሥልጠና ተሠጠ፡፡ በስልጠናው መክፈቻ የቋንቋ መምህራን ተማሪዎቻቸው ያሉበትን ደረጃ ጠንቅቀው በመረዳት ከመሠረታዊው የቋንቋ ክሂሎት በተጓዳኝ ቋንቋውን በፍላጎት እና በፍቅር እንዲማሩ፣ እንዲለምዱ እና እንዲናገሩ ማስቻል ለዚህም የቋንቋ […]
Read Moreየ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል ዛሬ ጥር 17 ቀን 2017 በአዘጋጁ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረ ሲሆን፣ በመክፈቻ ሥነስርዓቱም ላይ የኢፌዴሪ ትምህርት ሚንስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣የዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንቶች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና በርካታ ታዳሚዎች ተገኝተዋል። 49 ዩኒቨርሲቲዎችና ከ2500 በላይ ስፖርተኛ ተማሪዎች የሚሳተፉበት ውድድሩ በአምስት ዘርፎች ማለትም በአትሌቲክስ፣ በእግር ኳስ፣ በባህል ስፖርት፣ በቼዝ […]
Read Moreበኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና በአፋር ትምህርት ቢሮ . መካከል ዛሬ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም የተፈረመው ስምምነት፣ በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሚገኙ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማብቃት ሞዴል የትምህርት ተቋም ለማድረግ የሚያስችሉ የሥልጠና እና የምርምር ሥራዎችን በጋራ ለመስራት የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡ የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት፣ በሀገራችን የትምህርት መስክ ዘመናትን […]
Read Moreየኢ.ፊ.ዴ.ሪ ትምርህርት ሚኒስቴር ከሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቦርድ ሰብሳቢዎች እና ፕሬዚዳንቶች ጋር በየተልዕኮአችን ለ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም KPI: Performance Contract Agreement” መፈራረሙ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መነሻነትም ዛሬ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም በዩኒቨርስቲ ደረጃ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ከምክትል ፕሬዝዳንቶች እና ከጽ/ቤት ሃላፊ ጋር በየዘርፎቻቸው ካስኬድ በተደረጉ የበጀት ዓመቱ ዕቅድ ቁልፍ የውጤት አመላካቾች ላይ “Performance Contract Agreement” ተፈራርመዋል፡፡ በፊርማ […]
Read Moreየመማር ማስተማር ሂደትን ፣ የምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎትን በተመለከተ ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መምህራን ጋር በ04/03/2017 ዓ.ም በተደረገው ውይይት የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፈቀደ ቱሊ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሐሳብ፣ በዓለምዓቀፍ ደረጃ የሚታየው ለውጥ ፈጣን በመሆኑ መምህራን ጊዜውን የሚመጥን ክህሎት፣ ዕውቀትና አመለካከት እንዲኖራቸው ራሳቸውን በየጊዜው ማዘጋጀት እንዳለባቸው ገለጸዋል፡፡ለውጤታማ የመማር ማስተማር ሂደት መምህራን ሁልጊዜም ማንበብና ምርምር […]
Read Moreበ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ አልፋችሁ ለ2017 የትምህርት ዘመን ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ ህዳር 04 – 05 ቀን 2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ግቢ በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡
Read Moreበ 2017 ዓ.ም ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሰቲ በመጀመሪያ፣ ሁለተኛ ዲግሪ እና PGDT በኤክስቴንሽን እንዲሁም በዶክትሬት ዲግሪ ለመማር አመልክታችሁና ያለፋችሁ አመልካቶች ምዝገባ የሚከናወነው ከህዳር 13 – 15 ቀን 2017 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን …
Read Moreየኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ በ2016 ዓ.ም ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሁሉንም (100%) በከፍተኛ ውጤት ማሳለፍ መቻላችንን ስናበስር እጅግ ደስ እያለን ነው። የተመዘገበው ውጤት ተማሪዎችን ከታች ይዞ መኮትኮት ከተቻለ በትምህርት ስርዓቱ ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ ነው። የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ በአዲስ አበባ ከተማ ከ8ኛ ክፍል ወደ 9ኛ የሚሸጋገሩ ተማሪዎችን በመቀበል በዩኒቨርስቲው […]
Read Moreየኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ!” በተሰኘው ሀገራዊ መሪ ቃል የችግኝ ተከላ አካሄዱ፡፡ የችግኝ ተከላው በወንድይራድ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከላውን ያስጀመሩት ፕሬዘዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና ሀገርና ትውልድን ለማስቀጠል “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ!” በሚል ሀገራዊ መሪ ቃል እየተደረገ ያለውን የችግኝ ተከላ ማስቀጠል ከሁሉም የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በክቡር ጠቅላይ […]
Read More