ኮ.ት.ዩ. ሀገሪቱ የምትፈልጋቸውን የትምህርት ባለሙያዎች በጥራት እንዲያሰለጥን ትልቅ ኃላፊነት የተሰጠው ዩኒቨርሲቲ መሆኑ ተገለፀ፡፡

በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ዩኒቨርሲቲውን በጎበኙበት ወቅት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ እንደገለፁት፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ (ኮ.ት.ዩ.) ሀገሪቱ የምትፈልጋቸውን የትምህርት ባለሙያዎች በጥራት እንዲያሰለጥን ትልቅ ኃላፊነት የተሰጠው ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡
ሀገሪቱ ያለባትን የትምህርት ጥራት ችግር መፍታት ብቃት ያላቸውን የትምህርት ባለሙያዎችን እንዲያፈራ ትልቅ ኃላፊነት የተሰጠውን ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የሚገኝበትን አቋም ለመገምገም የመስክ ምልከታ ያካሄደ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ፣ ቋሚው የኮሚቴ አባላት ለመስክ ምልከታው ትልቅ ቦታ እንዳላቸውም አመልክተዋል፡፡
የመስክ ምልከታውን ትኩረት አስመልክቶ በተካሄደው ውይይት ወቅት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና እንዳሉት፣ ዩኒቨርሲቲው በነበረው የስያሜ፣ ተልዕኮ እና የአደረጃጀት ለውጥ፣ የቦታ ጥበት፣ በበጀት እና በመሠረተ ልማት ረገድ የተለያዩ ችግሮች ቢኖሩበትም ውጤታማ የሆኑ ልዩ ልዩ ሀገራዊ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም ከመስከረም 24/2014 ዓ.ም ጀምሮ ተቋሙ የተሰጠውን አዲስን ተልዕኮ በብቃት እንዲወጣ የሚያስችሉት ፍኖተ ካርታ እና ሥርዓተ ትምህርት የማዘጋጀት፣ የውጭ ሀገር ተሞክሮ የመቀመር፣ በውጭ እና በሀገር ውስጥ ዕውቅ ምሁራን የማስገምገም፣ ከተለያዩ ባለከድርሻ አካላት ጋር ውይይት የማካሄድ፣ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት እና የግንባታ ስራዎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ የተከናወኑ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ብርሃነመስቀል፤ አሁንም ቀሪ ስራዎች በትጋት እየተሰሩ ስለመሆናቸው ተናግራዋል፡፡
ከመነሻ ውይይቱም በኋላ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚገኙ የቤተመጻሕፍት፣ የተማሪዎች መኝታ ክፍል እና የመመገቢያ አዳራሽ፣ ክሊኒክ፣ የመማሪያ ክፍሎች እንዲሁም ነባር እና እየተሰሩ ያሉ የህንፃ ግንባታዎች በመስክ ምልከታው የተጎበኙ ሲሆን ከጉብኝቱ በኋላም ከዩኒቨርሲቲው መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡
በተደረገው ውይይትም ወቅት የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ መሠረተ ልማትና ለመማር ማስተማሩ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በተፈለገው ደረጃ አለመኖር እንደ ችግር የገለፁ ሲሆን፣ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ በሰጡት ምላሽም ዩኒቨርሲቲው ትልቅ የሰው ሃብት ስላለው ተስፋ የሚጣልበት በመሆኑ የተዘረዘሩት የቦታ ጥበት፣ የበጀት፣ የመሠረተ ልማት እንዲሁም የመምህራን ጥቅማ-ጥቅም እና የደመወዝ ችግሮች በሂደት እንዲፈቱ ቋሚ ኮሚቴው ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር ደረጃ በደረጃ እንደሚወያይ፣ ችግሮቹም እንደሚፈቱ ጠቅሰው እስከዚያው ድረስ ግን የመማር ማስተማሩ ሂደት በሰላማዊ መንገድ እንዲቀጥል መምህራን የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
                                            የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 7 people, people standing, people sitting and indoor

“ለኢትዮጵያ ልዕልና የምሁራን ሚና” በሚል መሪ ቃል የምሁራን መድረክ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ትብብር መዘጋጀቱ ተገለፀ፡፡

የሁለቱም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት፣ “ለኢትዮጵያ ልዕልና የምሁራን ሚና” በሚል መሪ ቃል የፊታችን ሰኞ ህዳር 26 ቀን 2015 ዓ.ም በኃይሌ ግራንድ ሆቴል የሚካሄደው የምሁራን መድረክ ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና እንዳሉት ይህ መድረክ ምሁራን በነፃነት የሚወያዩበት፣ የሃሳብ ልዕልና የሚፀባረቅበት፣ ለወቅታዊ ችግሮቻችን የሚበጁ ምክረ-ሃሳቦችም የሚቀርቡበት ይሆናል፡፡ በዚህ የምሁራን መድረክ ላይ ከ300 በላይ የሚሆኑ በዩኒቨርሲቲዎችና በተለያዩ የምርምር ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ ምሁራን እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የሚያሳተፉ ሲሆን፣ ሀገራዊ እና ዓለማቀፋዊ ጉዳዮችን የሚያስቃኙ ሁለት የውይይት መነሻ ጽሑፎች ቀርበው ምሁራዊ ውይይት እንደሚካሄድባቸውም ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና ተናግረዋል፡፡
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደረጀ እንግዳ የምሁራንን አቅም የመጠቀም ውስንነት እንደነበር ጠቅሰው ከአሁን በኋላ ግን የምሁራን ተሳትፎ ለማሳደግ ተከታታይ ውይይቶች እንደሚዘጋጁ አመልክተዋል፡፡
ተጋባዥ ምሁራን በዚህ መድረክ ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ሀገርን የሚያሻግር ሐሳብ በማቅረብ የዜግነት ድርሻቸውን እንዲወጡ ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና እና ዶክተር ደረጀ እንግዳ ጠይቀዋል፡፡
                               ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

KUE Conducts Its Roadmap and Curricula Validation at Ministerial Level

After a series of intensive hands-on calibrations at various stages, Kotebe University of Education (KUE) conducted validation of its roadmap and curricula at the ministerial level today, on the 12th of November 2022. Led by the state ministers, Samuel Kifle (PhD) and Fanta Mandefro (PhD), the endorsement convening involved teachers’ professional development and curriculum experts of the Ministry of Education of the Federal Democratic Republic of Ethiopia.
The state ministers were whole-heartedly in the favour of the efforts that have been undertaken by the University in paving the way to bring changes in the quality of education, and they unanimously underscored that the University should commence the execution of its plans taking the national education reform roadmaps and current education policy provisions into account.
It was also remarked that the University needs to consult and closely work with the experts of the Ministry to fine-tune the alignment of the national education policy and the existing demands of teachers and instructional leaders with the education professional workforce to be produced.
                           Communications Affairs Directorate

ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

09/03/2015 ዓ.ም
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
በሥነጽሑፍና ፎክሎር የኤም ኤ መርሃግብር መቀጠል ለምትፈልጉ ይህ
ማስታወቂያ ከተለቀቀበት ቀን ጀምሮ እስከ ሕዳር 15/2015 ዓ.ም ድረስ
በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ድረገጽ ላይ በመግባት በኦንላይን (https://estudent.kmu.edu.et/auth/login)መመዝገብ
የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
በቋንቋዎችና ስነሰብ ፋካሊቲ
የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ ትምህርት ክፍል

 

ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

ማስታወቂያ

ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ድግሪ ፤በሁለተኛ ድግሪ በቀን ፣ በማታና  ቅዳሜና እሁድ  ፕሮግራም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰተማር ይፈልጋል፡፡ሰለሆነም ከታች በተዘረዘሩት የትምህርት መስኮች ከህዳር 1 እስከ ህዳር 15/03/2015ዓ.ም በኦላይን (Online) መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን  የመመዝገቢያ ክፍያ በCBE Birr  ብቻ በመከፈል ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

 ለመመዝገብ በዩኒቨርሲቲው ድህረ ገፅ

How to Pay:

CBE Birr

    • Dial *847#
    • Choose  Pay Bill
    • Choose  Webirr
    • Enter the above Payment Code
    • Finally Approve

ለማመልከት የሚስፈልጉ መስፈርቶች

ለሁለተኛና ሶስተኛ ድግሪ

    • ተዛማጅ በሆነ የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪ/የሁለተኛ ዲግሪ ሰርተፍኬት እና ትራንስክርፒት Scan ተደርጎ በ PDF ፋይል በሲስተሙ ላይ Upload ማድረግ
    • ለመመዝግቢያ ብር 100 አንድ መቶ ብር ሲስተሙ በሚሰጠው ኮድ በ CBE Birr. መክፈል

 መግቢያ ፈተናውን ያለፉ ከምዝገባ በፊት

    • Letter of Recommendation ከአሰሪ ተቋም /በመስረያ ቤት ስፖንሰር ለሚማሩ ተማሪዎች /ፎርምን ከዩኒቨርሲቲያችን መረጃ መረብ https://www.kue.edu.et ማውረድና በመሙላት ለዩኒቨርሲቲ ማቅረብ የሚችል፡፡
    • ከተማሩበት ዩኒቨርሲቲ Official Transcript ማስላክ
    • የመጀመሪያ ዲግሪ ሰርተፍኬት እና ትራንስክርፒት ኮፒ የማይመለስ ከዋናው ጋር በማመሳከር ከአንድ ክላሴር ጋር ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡

ለመጀመሪያ ድግሪ

    • በትምህርት ሚኒስተር የተቆረጠውን የመግቢያ ነጥብ የሚያሞላ የ12ኛ ክፍል ስርተፍኬት Scan ተደርጎ በ PDF ፋይል በሲስተሙ ላይ Upload ማድረግ፡፡
    • ተዛማጅ በሆነ የትምህርት መስክ በደረጃ 4 የተመረቀ ከሆነ ዲፕሎማውን፣ ትራንስክሪፕትና የብቃት ማረጋገጫ እና 2(ሁለት) ዓመት የስራ ልምድ ማሰረጃ Scan ተደርጎ በ PDF ፋይል በሲስተሙ ላይ Upload ማድረግ፡፡
    • ተዛማጅ በሆነ የትምህርት መስክ የመምህርነት ዲፕሎማና ትራንስክሪፕት Scan ተደርጎ በ PDF ፋይል በሲስተሙ ላይ Upload ማድረግ፡፡
    • የመመዝገቢያ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) ሲስተሙ በሚሰጠው ኮድ በ CBE Birr መክፈል

መግቢያ ፈተናውን ያለፉ ከምዝገባ በፊት

    • የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር
    • የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ትራንስክርፒት ከማይመለስ ፎቶ ኮፒ
    • የ12ኛ ክፍል ስርተፍኬት ከማይመለስ ኮፒ ጋር በማመሳከር ከአንድ ክላሴር ጋር ማቅረብ በአካል ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡
    • በደረጃ 4 የተመረቀ ከሆነ ዲፕሎማውን፣ ትራንስክሪፕትና የብቃት ማረጋገጫ እና 2(ሁለት) ዓመት የስራ ልምድ ማሰረጃ ከዋናው ጋር በማመሳከር ከአንድ ክላሴር ጋር ማቅረብ በአካል ማቅረብ ያስፈልጋል፡፡
    • በደረጃ 4 እና በዲፕሎማ ለተማሩ ከተማሩበት ተቋም Official Transcript ማስላክ ማስመጣት ግዴታ ነው፡፡

 

Post Graduate Diploma in Teaching – (PGDT) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ

 

    • በማስተርስና በድግሪ የተመረቃችሁ መሆን አለባችሁ እንዲሁም የትምህርት ማሰረጃ Scan ተደርጎ በ PDF ፋይል በሲስተሙ ላይ Upload ማድረግ፡፡
    • ለመመዝግቢያ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) ሲስተሙ በሚሰጠው ኮድ በ CBE Birr.

 

የትምህርት ፕሮግራሞች

 

Second Degree and Third Degree Programs Registration Modality
College of Language Education and Literature 1.DED in English Language Teaching Regular
2.Master of Education in ELT Regular, Evening and weekend
3.Master of Education in Teaching Amharic Regular, Evening and weekend

 

 

 

 

4.Master of Education in Literature
5.Master of Education in Oromo Language and

Literature

Faculty of Business and Economics 1.MSC in Economics Regular, Evening and weekend
2.Master of Business Administration (MBA) Regular, Evening and weekend
3.MSC in Accounting and Finance
College of Science and Mathematics Education 1.PhD in Statistics Regular
2.Master of Education in Biology Regular, Evening and weekend
3.Master of Education in Chemistry
4.Master of Education in Physics
5.Master of Education in Mathematics
6.MSC in Computer Science
7.MSC in Statistics
Institute of Physical Education and Sport 1.Master of Education in Physical Education and Sport Regular, Evening and weekend
2.MSC in Football Coaching Regular, Evening and weekend
3.MSC in Athletics Coaching
4.MSC in Sport Management
5.MSC in Exercise Physiology Regular, Evening and weekend
College of Educational Sciences 1.DEd in Curriculum and Instructional  Regular
2.DEd in Educational Policy and Strategic

Management(Regular Program)

Regular
3. Master of Education in in Counseling Psychology
4.Master of Education in Special Needs and Inclusive Education
5.Master of  Educational in Educational Psychology Regular, Evening and weekend
6.MEd in Educational Leadership and Management Regular, Evening and weekend
  7. Master of  Educational in Curriculum and Instructional Technology Regular, Evening and weekend
College of Social Science Education 1. DED in Geography and Environmental Education Regular
2.Master of Education in History Regular, Evening and weekend
3.Master of Education in Civics and Ethics Education
4.Master of Education in Geography and

Environmental Studies

5.MA in Urban Socio-Economics Development

 

6.MA in Social Work Regular, Evening and weekend
7.MA in Disaster and Risk Management Regular, Evening and weekend
“Faculty of Urban Development Studies”

 

1.MSC in Environmental Management Regular, Evening and weekend
2.MSC in Transport Planning and Management Regular, Evening and weekend
3.MSC in Land Management and Tenure Regular, Evening and weekend

 

 

 

 

First Degree Programs
College Field of Specialization Registration Modality
College of Social Science Education 1.BEd Civics and Ethics Education Regular, Evening and weekend
2. BEd Social Studies Geography and Environmental Education Regular, Evening and weekend
3. BEd in Social Studies (History) Regular, Evening and weekend
College of Science and Mathematics  Education 1.BEd in Mathematics Regular, Evening and weekend
2.BEd in General Science (Biology)

 

Regular, Evening and weekend
3.BEd in General Science (Chemistry) Regular, Evening and weekend
4.BEd in General Science (Physics) Regular, Evening and weekend
5.BEd in Information Technology Regular, Evening and weekend
College of Languages and Literature   Education 1.BEd in Amharic Language and Literature Regular, Evening and weekend
2.BEd in Oromo Language and Literature Regular, Evening and weekend
3.BEd in English Language and Literature Regular, Evening and weekend
College of   Educational Sciences 1.BEd in Special Needs and Inclusive Education Regular, Evening and weekend
2.BEd in Early Childhood Development and Education Regular, Evening and weekend
3.BEd in Educational Leadership and Management Regular, Evening and weekend
4.BEd in Educational Psychology Regular, Evening and weekend
Institute of Physical Education and Sport 1.BEd in Physical Education and Sport Regular, Evening and weekend
Post Graduate Diploma in Teaching (PGDT )Program
College Field of Specialization Registration Modality
College of   Educational Sciences 1.PGDT Training Regular, Evening and Weekend
       

 

ማሳሰቢያ

  • የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በግል ዩኒቨርሲቲ የተማሩ ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን መስሪያ ቤት የትምህርት ማስረጃው ትክክለኛነት ማረጋገጫ እንዲኖረው ይገባል፡፡
  • Phd and DEd Program  በቀን  ብቻ የሚከፈቱ ናቸው፡፡

KUE Conducts Oromo Language and Literature Curricula Validations

The Department of Oromo Language, Literature, and Communications of Kotebe University of Education got validated two curricula, undergraduate and postgraduate programmes today, on the 26th of October 2022. The curricular documents for both undergraduate and postgraduate programmes have been reviewed by highly qualified and experienced reviewers from renowned universities – two external and one internal reviewers for each curriculum were identified and invited to carry out the validation.
                                 Communications Affairs Directorate
May be an image of 12 people and people standingMay be an image of 1 person, beard, sitting and indoorMay be an image of 1 person, sitting and standingMay be an image of 5 people and people standingMay be an image of 5 people, people sitting and indoorMay be an image of 7 people, people sitting and indoor
 

ማስታወቂያ ! ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎች በሙሉ

የ2015 ትምህርት ዘመን የነባር የድህረ-ምረቃ፣ መጀመሪያ ዲግሪና የዲፕሎማ  የቀን፣የማታና የእረፍት ቀናት ተማሪዎች (ከ2ኛ አመት ድህረምረቃ ፕሮግራም በስተቀር) የአንደኛ ሴሚስተር ምዝገባ  ከጥቅምት 28 – 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚከናወን መሆኑን እያስታወቅን በተጠቀሱት ቀናት ‘’online’’ ምዝገባ እንድታከናውኑ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ

    • የድህረ-ምረቃና የ “Extension” ተማሪዎች የምዝገባ ክፍያ ስርአት ሙሉ በሙሉ የሚከናወነው በ online  CBE Birr  መሆኑን፣  በደረሰኝና በባንክ አካውንት የማናስተናግድና  በደረሰኝና በባንክ አካውንት ለምዝገባ የተከፈለ ክፍያ ተቀባይነት የማይኖረው መሆኑን
    • ከምዝገባ በኋላ ባሉት 10 ቀናት ውስጥ የቀድሞው የተማሪዎች መታወቂያ የሚቀየር ስለሆነ በሲስተሙ ፕሮፋይላችሁ ላይ ለመታወቂያ የሚሆን ፎቶ ግራፍ(3 ×4) ከወዲሁ እንድታስገቡና ከየኮሌጁ/ፋካሊቲ/አካዳሚ በመጠየቅ መታወቂያችሁን እንድታስቀይሩ
    • የ2015 ትምህርት አንደኛ ሴሚስተር ትምህርት  ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚጀምር መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

ሬጅስትራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት

በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ

ጥብቅ ማስታወቂያ

                                            **************

በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ

ውድ ተፈታኞች በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ወደ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ስትመጡ መያዝ የተፈቀደላችሁ ቁሳቁሶች ብቻ ይዛችሁ እንድትመጡ በጥብቅ እናሰስባለን፡፡

    1. ተፈታኞች እንዲይዙ የተፈቀደላቸው ቁሳቁሶች

Ø መጻሕፍት እና ሲያጠናቿው የነበሩ ማስታወሻዎች

Ø ልብስ የሌሊት፤ ልብሶችን ጨምሮ (አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ የመሳሰሉት)፣

Ø የመፈተኛ ካርድ፣ እርሳስ፣ ላጲስ፣ መቅረጫ

Ø የግል ንጽህና መጠበቂያዎች (ሳሙና፣ ሞዴስ… የመሳሰሉት)

Ø ገንዘብ (ብር)

Ø ደረቅ ምግብ ብቻ ናቸው፡፡

    1. ተፈታኞች እንዳይዙ የተከለከሉ ቁሳቁሶች

Ø ማንኛውም የኤሌክትሮኒክስ ዕቃ (ቪዲዮ፣ የፎቶራፍ ካሜራ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላብቶፕ፣ስልክ፣ አይፖድ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ፍላሽ፤ ማጂክ ጃኬት እና የመሳሰሉት) ናቸው፡፡

Ø ከጋብቻ ቀለበት ውጪ ማንኛውም ቀለበት፣ ማንኛውም ጌጥ፣ ሰዓት፣ ሃብል፣ የጸጉር ጌጥ ወዘተ

Ø መነፅር (ከዕይታ ችግር ጋር በተያያዘ በሃኪም የተፈቀደ ካልሆነ በስተቀር)

Ø የሃኪም ማዘዣ የሌለው መድኃኒት

III. ተፈታኝ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ወቅት የሚጠበቁባቸው ተግባራት

Ø ማንኛውም ተፈታኝ የዩኒቨርሲቲውን ሕግና ደንብ ተከትሎ የፈተናውን ጊዜ ማሳለፍ ይጠበቅበታል፡፡

Ø ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ የፈተና ህግና ደንቦችን በአግባቡ ማክበር ይጠበቅበታል፡፡

Ø ማንኛውም ተማሪ ከሌሎች ተፈታኞች ጋር በወንድማማችነትና በእህትማማችነት መንፈስ በሰላም የፈተናውን ጊዜ ማሳለፍ ይኖርበታል፡፡

Ø ማንኛውም ተማሪ በፈተና ጊዜ ካልሆነ በስተቀር ወደ መፈተኛ ክፍሎች መግባት አይኖርበትም፡፡ ከፈተና ሰዓት ውጪ ተፈታኞች ከማደሪያ ክፍሎቻችው ወይም ከተፈቀዱላቸው ሌሎች አካባቢዎች ውጪ መንቀሳቀስ አይፈቀድላቸውም፡፡

Ø ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ የመመገቢያ እና የፈተና ሰዓትን በአግባቡ ማክበር ይኖርበታል፡፡

Ø ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጠጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት አይችልም፡፡

Ø ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ በፈተና ሰዓት፣ በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም አይችልም፡፡

Ø የማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ወላጆች፣ አሳዳጊዎችም ሆኑ ሌላ ቤተሰብ በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ እንዲገቡ አይፈቀድም፡፡

Ø ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልም ይሁን መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ፣ የትምህርት ቤት ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ የመገኛት ግዴታ አለበት ፡፡

Ø ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ አለበት፡፡

                                                                                                    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት የበጎ ፈቃደኝነት ቀን የሆነውን ጳጉሜ አንድ ምክንያት በማድረግ ችግኝ ተከሉ፡፡

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት የበጎ ፈቃደኝነት ቀን ምክንያት በማድረግ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ በተዘጋጁ ስፍራዎች ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ፍራፍሬ ችግኞችን ጭምር ዛሬ ጳጉሜ 1/2014 ዓ.ም ተክለዋል፡፡
የችግኝ ተከላው ስነስርዓት በተጀመረበት ወቅት የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና፣ ጳጉሜ አንድ ቀን የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በመሆኑ ወደን ፈቅደን የምንሰራበት፣ ወደን ፈቅደን ችግኝ የምንተክልበት፣ ወደን ፈቅደን ሀገራችንን ከወራሪው ኃይል የምንከላከልበት ቃል የምንገባበት ነው ብለዋል፡፡ ወንድሞቻችን የመከላከያ ሠራዊት አባላት በግንባር እየተፋለሙ እና ለሀገራቸው የህይወት መስዋዕት እየከፈሉ መሆናቸውን የጠቀሱት ፕሬዝዳንቱ፣ እኛ ደግሞ በአንድ በኩል ልማቱን እያሳለጥን በሌላ በኩል ለሀገር መከላከሉ ደጀንነታችንን የምናረጋግጥበት ነው ብለዋል።
ዛሬ የምንተክለው ችግኝ ከተንከባከብነው ለትውልድ የሚተላለፍ፣ ድርቅን በመከላከል የሀገራችን ምህዳር የተሻለ የሚያደርግ ጠቀሜታውም ዘርፈ ብዙ ነው ያሉት
ዶ/ር ብርሃነመስቀል አያይዘው የወለደችንና ያሳደገችን እናት ሀገራችን ለኛ ችግኛችን ናት ልንጠብቃት ልንንከባከባት ይገባል ለዚህም በዚህ አጋጣሚ በግንባር ሆኖ መስዋዕትነት እየከፈለ ካለው መከላከያችን ጎን መሆናችንንና ለሚጠበቅብን ሁሉ አለኝታችንን እናረጋግጣለን ብለዋል።
በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የግቢ ውበት እና መናፈሻ ሥራ ኃላፊ አቶ ግርማ ከፍያለው በዚሁ ጊዜ ስለ ችግኝ አተካከል ገለፃ የሰጡ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት የተተከሉትን 600 ችግኞች ጨምሮ በዘንድሮው ዓመት 18 ሺህ ልዩ ልዩ ችግኞች በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡
ከተተከሉት ችግኞች መካከል ጓሳ የተሰኘ የሣር ዝርያን ጨምሮ አፕል (ፖም)፣ አቦካዶ፣ ፅድ፣ አልተርናታ፣ ሳይፕረስ እና ስፓቶዲያ እንደሚገኙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
                                     ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 6 people, people standing, tree and grassMay be an image of 5 people, people standing and outdoors

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተቋማዊ የሽግግር ሰነዶች ላይ ከመምህራን ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተቋማዊ የሽግግር ሰነዶች ላይ ከመምህራን ጋር ዛሬ 23/12/2014 ዓ.ም. በዋና ግቢ ውይይት አካሄዷል፡፡ የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት አብይና ቴክኒካል ኮሚቴ ተዋቅሮ ሰፋ ያለ ጊዜ ተወስዶ ሲዘጋጅ የቆየው የዩኒቨርስቲው ምስረታ ፍኖተ ካርታው እና የካሪኩለም ማዕቀፍ ከመነሻው ጀምሮ ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ ሁኔታ እንዲሆን ተደርጓል። በዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና የዘርፉ ከፍተኛ ምሁራን፣ የቦርድ አመራሮች ፣ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል ወዘተ ተወያይተውበት ግብዓት ሰጥተውበታል።
ፕሬዚዳንቱ አያይዘው እንዳሉት እየተዘጋጀ ያለው ፍኖተ ካርታ እና የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ በአጠቃላይ የሀገሪቱን የትምህርት ጥራት ችግር እና ክፍተት ለመሙላት ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ከራሳችን ጀምረን ክፍተቱን የሚያርም ዝግጅት ማድረግ ይጠበቅብናል፤ በመሆኑም የዩኒቨርሲቲው መምህራን ለአዲሱ ተልዕኮአችን ብቁነታቸውን ማረጋገጥ ፤ ራሳቸውን ማዘጋጀት ፤ “ማነው መምህር ?” የሚለውን መመለስ ይጠበቅባቸዋል። ለዚህ መሠረታዊ ጉዳዩ ከቀደመው አስተሳሰብ ወጥቶ በአዲስ እይታ አዲሱን ሀገራዊ ተልዕኮና ኃላፊነት በአዲስ አስተሳሰብ መቀበልና ለዚያ ትግበራ ብቁ ሆነው ለመገኘት የትምህርት ዩኒቨርሲቲዎችን ልምድ ማየትና መረዳት አለብን ብለዋል ።
ለስኬቱም ተቋሙ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች፣ የትምህርት ቢሮዎች ፣ የፌዴራል እና የክልል የሥልጠና ተቋማት ቀጥተኛ ባለድርሻዎቻችን ናቸው። ከዚህም አንፃር ከባለድርሻ አካላቱ እንዲሁም ከዘርፉ ምሁራን ጋር ቅንጅት በመፍጠር የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮንም በመቀመር ሰነዶቹን የበለጠ ማዳበር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ጊ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሽመልስ ዘውዴ እንደተናገሩትም፣ ዩኒቨርሲቲው አዘጋጅቶ በተለያዩ መድረኮች ለባለድርሻ አካላት ለውይይት ካቀረባቸው ሰነዶች መካከል የተቋሙ የሽግግር ፍኖተ ካርታ እና የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍ ላይ የዩኒቨርሲቲው መምህራን እንዲወያዩባቸው መድረኩ የተዘጋጀው ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ትግበራ የሚገባ በመሆኑ መምህራኑ በቂ ግንዛቤ በመጨበጥ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለማስቻል እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ዶ/ር ፈቀደ ቱሊ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ የተቋሙ የሽግግር ፍኖተ ካርታ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ብቸኛው የሀገሪቱ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን በአዋጅ ከተወሰነበት ጊዜ ጅምሮ በተሰጠው ኃላፊነት መሠረት ሰነዱ የትምህርት ጥራት ችግርን በሚፈታ እና ሁለንተናዊ የትምህርት አካሄድን በሚያግዝ መልኩ መዘጋጀቱን ለውይይቱ ተሳታፊዎች አብራርተዋል፡፡ ዶ/ር ኤፍሬም ተክሌ በበኩላቸው የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፉ የዩኒቨርሲቲውን አጠቃላይ የመማር ማስተማር ሂደት የሚመራ ሲሆን፣ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር መዘጋጀቱን እና በተለያዩ ባለድርሻ አካለት በተለያዩ ጊዜያት ውይይት የተደረገበት መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው መምህራንም በበኩላቸው በቀሩት የዩኒቨርሲቲው ተልዕኮ፤ የትምህርት መርሀግብሮችና ስያሜዎቻቸው እንዲሁም በተማሪዎች አቀባበል ሁኔታዎች ላይ በማተኮር ሰፊ ገንቢ ሀሳቦችን በማንሳት በውይይቱ ላይ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል፡፡
                                የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
May be an image of 3 people, people sitting and indoorMay be an image of 7 people and people sitting