Category Archives: Uncategorized
የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ እንደቀድሞው ሁሉ ዘንድሮም በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸውን ተማሪዎች የላቀ ውጤት አስመዝግቧል ።
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያለው ጠንካራ ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለጸ፡፡
The Second Round KUE-CUE ICT and Science Teachers in-Service Joint Training Concluded Successfully
The Second Round KUE-CUE ICT and Science Teachers in-Service Joint Training that was spanned from August 26-30, 2024, for five consecutive day was successfully concluded on Friday August 30, 2024. The training aims at strengthening the capacity of Science and ICT education teachers through targeted in-service training programs.
On the opening event, Dr. Dejen Chaka welcomed the Korean delegation, KUE Instructors and the teacher trainees on behalf of Dr. Berhanemeskel Tena, the President of Kotebe University of Education. Dr, Dejen remarked on this event that To date, this initiative has successfully reached 18 secondary and 41 elementary schools in total 59 schools within Addis Ababa City Administration. As a result, 148 Science and ICT teachers have benefited from this program which enhances their skills and knowledge to better serve their students, and of course your nation.
Professor Kim Hyun Joo, the General Manager of the 2023 Civil Society Partnership Program/KOICA Project, welcomed instructors and trainee teachers to the second round of teacher training held at KUE from August 26-30, 2024. She expressed gratitude to Dr. Berhanemeskel Tena, President of Kotebe University of Education, for his collaboration and to Dr. Dejen Chaka, the Coordinator, and the project team for their dedication. Professor Kim noted the historical support of Ethiopian soldiers during the Korean War and emphasized the importance of mutual aid, stating that Korea now aims to support Ethiopia. Additionally, she expressed optimism about achieving shared goals and producing successful students through the hard work of the trained teachers.
It was evidenced that the training initiated through the 2023 Civil Society Partnership Program (2023 CSPP/KOICA) supported by KOICA financially.
Kotebe University of Education Concluded Training for Trainers of Trainees
Kotebe University of Education has successfully concluded training for Trainers of Trainees, equipping them to lead a summer capacity building initiative for secondary school teachers and school leaders. The training, which commenced yesterday and concluded today, July 24, 2024, aimed to bolster the skills and knowledge of educators across the nation.
During his closing remarks, Dr. Berhanemeskel Tena, President of Kotebe University of Education, expressed his confidence that the training had provided participants with the necessary tools for success. He emphasized the importance of discipline and accountability throughout the training process, highlighting that this program represents a significant investment by the government, particularly the Ministry of Education.
The upcoming summer capacity building training for secondary school teachers and school leaders, scheduled to begin on July 29, 2024, will be closely monitored by a task force chaired by the University President.
Public and International Relations Office
የ2016 ዓ.ም ልዩ የክረምት መርሐግብር የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመውሰድ በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ሰልጣኞች በሙሉ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር ለልዩ የክረምት መርሐግብር የአቅም ግንባታ ስልጠና እንድትወስዱ በዩኒቨርሲቲው የተመደባችሁ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ምዝገባ እንደሚካሄድ አውቃችሁ፣ በዕለቱ በዩኒቨርሲቲው በአካል በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ከተጠቀሰው ዕለት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ሰልጣኝ በምንም ሁኔታ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ
ወደ ዩኒቨርስቲው ስትመጡ ፦
-
- ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ
- ከኦሮሚያ የምትመጡ ሰልጣኞች የራሳችሁን ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና የትራስ ጨርቅ መያዝ ይኖርባችኋል፡፡
- ከአዲስ አበባ የምትመጡ በተመላላሽነት ስለምትስተናገዱ የተጠቀሱትን ጉዳዮች ማምጣት አይጠበቅባችሁም።
- ከኦሮሚያ የምትመጡ ሰልጣኞች በዕለቱ ከ 2:30-3:30 ከአዲስ አበባ የምትመጡ ደግሞ ከ6:30 -7:30 ሰዓት በዩኒቨርሲቲ ግቢ ተገኝታችሁ ምዝገባ እንድታከናውኑ ፤
- ከአዲስ አበባ የምትመጡ ለመኝታ እና ለምግብ የተያዘላችሁ በጀት በካሽ የሚሠጣችሁ ይሆናል።
ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ፣ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎችን በታሪካዊው የዓድዋ መታሰቢያ ሁለገብ አዳራሽ በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ፡፡
ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ. ም
በመማር ማስተማር ሂደት ስድስት አስርት ዓመታትን ያስቆጠረው አንጋፋው ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ፣ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 868 ወንድ፤ 812 ደግሞ ሴት፤ በድምሩ 1680 ተማሪዎችን በታሪካዊው የዓድዋ መታሰቢያ ሁለገብ አዳራሽ ከፍተኛ የመንግሰት አመራሮች፣ ዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢና የቦርድ አባላት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና የሴኔት አባላት በተገኙበት በደማቅ ስነ-ስርዓት አስመረቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና በምረቃ ስነ-ስርዓቱ መክፈቻ ባስተላለፋት መልዕክት ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ፣ በመማር ማስተማር ሂደት በርካታ ውጣ ውረዶችን በማለፍና አያሌ ስኬቶችን በማስመዝገብ ለዚህ ደረጃ መድረሱን ጠቆመው መንግሥትም የአገሪቷን የትምህርት ችግር ለመቅረፍ ካለው ፅኑ ፍላጎት በመነሳት መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 1263/2014 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተወሰነው ውሳኔ መሠረት “ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ” በሚል ስያሜ በአዲስ መልክ እንዲደራጅ መደረጉንና በአሁኑ ወቅትም ብቸኛ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መሆኑንና አመልክተዋል፡፡
እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለፃ፣ ሀገሪቱ የምትፈልገውን የተማረ የሰው ኃይል በሟሟላት ረገድ ዩኒቨርሲቲው የበኩሉን አስተዋፅዖ ሲያበረክት የቆየ ሲሆን፣ አሁንም መንግሥት በሰጠው ልዩ ተልዕኮ መሠረት የትምህርት ስብራቱን ለመጠገን በአዲስ አወቃቀርና አደረጃጀት ፍኖተ ካርታ ነድፎና አዲስ የካሪኩለም ማዕቀፍ ቀርጾ የተሻሉ የትምህርት ባለሙያዎችን ለማፍራት ከምንጊዜውም በላይ እየተጋ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
የዕለቱ የክብር እንግዳ፤ የመንግስት የኮሚዩኒኬሸን ሚንስትርና የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰበሳቢ ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፤ ለተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሀገራችን በምታደርገው የብልፅግና ጉዞ ዋነኛ መሣሪያው ትምህርት በመሆኑ መንግሰት የትምህርት ተቋማትን ከማስፋፋት በዘለለ በትምህርት ጥራት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፤ በመቀጠልም ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ “እየገነባን እናስተምራለን፤ እያስተማርን እንገነበለን“ በሚል መሪ ቃል በአዲስ የለውጥ ጎዳና ላይ እንደሚገኝ ተናግረው፣ ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ጥራት፣ በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት ረገድ እየሠራ ያለው ተጨባጭ ውጤታማ ስራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ተቋሙ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣም ምሩቃንም በሥነምግባር የታነፁ ከአድልኦ የፀዱ ሁሉንም እኩል የሚያገለግሉ የመልካም ስብዕና ተምሳሌት እንዲሆኑ እና ከሙስናና ከብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ አሳስበዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር ለ2016 ዓ.ም እጩ ተመራቂ ተማሪዎች የተዘጋጀውን የመውጫ ፈተና ለተማሪዎቻቸው ከፍተኛ ሙያዊ እገዛ በማድረግ ተማሪዎቻቸው ፈተናውን ሙሉ በሙሉ እንዲያልፉ ላደረጉ ኮሌጆችና ትምህርት ክፍሎች የእውቅና ሰርቲፊኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡
ከፍተኛ ውጤት ላመጡ የቅድመ ምረቃና የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ሽልማት፣ የምስክር ወረቀትና የእውቅና አሰጣጥ ስነስርዓት የተከናወነ ሲሆን፣ 37 A+ በድምሩ 3.99 ነጥብ በማስመዝገብ እጅግ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገበች ሴት ተማሪ ዩኒቨርሲቲው ልዩ ሽልማት እና የሁለተኛ ዲግሪ ሙሉ ስኮላርሺፕ ያበረከተላት ሲሆን በተመሳሳይ 36 A+ በድምሩ 3.99 ነጥብ በማስመዝገብ እጅግ ከፍተኛ ውጤት ላመጣ አንድ ወንድ ተማሪ ዩኒቨርሲቲው የሁለተኛ ዲግሪ ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
የሕዝብና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት